የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ አህመድ መሀመድ ቡህ የ6ኛውን አገር አቀፍ ምርጫ በስኬት መጠናቀቅ አስመልክተው መልእክት አስተላልፈዋል::

    #ድሬዳዋ ስልጡን ሕዝብ – ስልጡን ከተማ የድሬዳዋ ሕዝብ ለሚቀጥሉት አምስት አመታት ይወክሉኛል ይመሩኛል ያላቸውን ተወካዮቹን ያለአንዳች ኮሽታ በመምረጥ ተደጋግሞ እንደሚባለውም ስልጡን ሕዝብ መሆኑን አስመስክሯል። 6ኛው አገራዊ ምርጫ በቅድመ ምርጫው ሂደትና በምርጫው እለት ያለምንም ችግር ሊከናወን የቻለው በሕዝባችን አገር ወዳድነትና አርቆ አስተዋይነት በመሆኑ በከተማም በገጠርም ለሚኖሩ ለመላው የአስተዳደራችን ነዋሪዎች ላቅ ያለ ምስጋናዬን አቀርባለሁ። በተጨማሪም ይሔ ምርጫ…

    Read More

      6ተኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በድሬዳዋ አስተዳደር ሰላማዊ በሆነ መንገድ መከናወኑን የድሬዳዋ ፖሊስ ኮምሽን ገለጸ፡፡

      ኮምሽኑ በዛሬው እለት 6ተኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በሰላም መጠናቀቁን አስመልክቶ ለተለያዩ የሚዲያ አካላት መግለጫ ሰተዋል፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር ፖሊስ ኮምሽን ኮምሽነር አለሙ መግራ በመግለጫቸው እንደተናገሩት የድሬዳዋ አስተዳደር ፖሊስ ኮምሽን ከምርጫ በፊት አቅዶ ወደ ስራ መግባቱን አስተውሰው በዚሁ መሰረት ምርጫው በተካሄደባቸው ሁሉም የከተማ እና ገጠሩ ቀበሌዎች ምርጫው ያለምንም የፀጥታ ችግር በሰላም ተካሄዶ መጠናቀቁን ተናግረዋል፡፡ ከተለያዩ የጸጥታ አካላት…

      Read More

        በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ድምፅ እንዳይሰጥባቸው ተከልክለው የነበሩ 6 የምርጫ ጣቢያዎች ድምጽ እንዲሰጥባቸው ምርጫ ቦርድ ወሰነ።

        በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ድምፅ እንዳይሰጥባቸው በብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ተከልክለው የነበሩ 6 የምርጫ ጣቢያዎች በዛሬው እለት ድምፅ እንዲሰጥባቸው የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ወስኗል። እነዚህ 6 የምርጫ ጣቢያዎች የመራጮች የምዝገባ ሂደት ከምርጫ ቦርድ እውቅና ውጭ አካሂደዋል ተብሎ ነበር ምርጫ እንዳይካሄድባቸው ውሳኔ የተሰጠው። የምርጫ ተወዳዳሪ ፓርቲዎችና ህብረተሰቡ ባቀረቡት ቅሬታና ጥያቄ መሰረት መራጮች የመምረጥ ዴሞክራሲያዊ መብት ስላላቸው ምርጫ ቦርድ በእነዚህ…

        Read More