የዘንድሮው 6ኛው አገራዊ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ እንዲሁም ዲሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እንዲካሄድ አስተዋጽኦ ለነበራቸው አካላት በተለይም ደግሞ ለመላው መራጭ ህዝብ የምሰጋና ስነስረአት ተካሂዷል።
በስነስረአቱ ላይ የድሬደዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ አህመድ መሃመድ ቡህ በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ የተለየ ስፍራ ያለው መሆኑን ገልፀው ዜጎች የሚወክላቸውን በፍላጎታቸው የመምረጥ ህገ መንግስታዊ መብታቸውን መጠቀም መቻላቸውን ገልፀዋል። 10 ፓርቲና 2 የግል ተወዳዳሪ እንደ ድሬደዋ በምርጫው መሳተፋቸውን፣ ምርጫው ውጤታማ እንዲሆን በርካታ አካላት ያሳዩት ተሳትፎ ዲሞክራስያዊ ስረአትን ለመገንባት በተለይም ከምንም በላይ ሃገርን የማስቀደም ዝንባሌ በዳበረ መልኩ…


