የዘመቻ ጥሪ
የኮቪድ አደገኛ ዝርያ የሆነው የዴልታ ቫይረስ፣ የችኩጉኒያ፣ የደንጊ ና የወባ በሽታ ስርጭት እየጨመረ በመምጣቱ የተነሳ ከፍተኛ የመከላከል ስራ መሰራት እንዳለበት በድሬዳዋ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ የሚመራ ግብረሃይል ገምግሞ አቅጣጫ አስቀምጧል:: በዚህም ሁሉም የአስተዳደሩ ነዋሪዎችና ሰራተኞች በየሳምንቱ የመኖሪያ አካባቢያችንን እና የመስራያ አካባቢያችንን በሚገባ ማፅዳት ይኖሮብናል:: በድሬዳዋ አዲሱ አስተዳደር ከተዋቀረበት ጊዜ ጀምሮ የአስተዳደሩ ከንቲባና ካቢኔአቸው የአስተዳደሩን ነዋሪዎች በማስተባበርና…


