ጥብቅ ማስጠንቀቅያ ለድሬዳዋ ነዋሪዎች በሙሉ

    በድሬዳዋ አስተዳደር ዴልታ በመባል የሚታወቀውና በዓለማችን ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ ያለው የኮቪድ ዝርያ ፣ እንዲሁም ደንጊ ፣ ቺክንጉኒያ እና ወባ አሳሳቢ በሚባል ደረጃ ተከስቷል ፡፡ ከዚህ ተደራራቢ ችግር ልንወጣ የምንችለው ማህበረሰባችን አሁን ያለንበትን ሁኔታ ተረድቶ እንደ አንድ ሆኖ የሚከተሉትን እርምጃዎች ሲወስድ ብቻ ነው ፡፡
    እነሱም ፡-
    1ኛ. ከቤታችን ውጪ ስንንቀሳቀስ የፊት ማስክ መልበስ ፣ አካላዊ እርቀታንን መጠበቅና እጆቻችንን ቶሎ ቶሎ መታጠብ ፣
    2ኛ. ዘወትር አካባቢያችንን ማጽዳት፣ ንፅህናዉን በሚገባ መጠበቅና ውሃ ያቆሩ ቦታዎችን ማፋሰስ ፣
    3ኛ. ከትንኝ ንድፊያ የሚመጡ በሽታዎችን ለመከላከል በጸረ ትንኝ መድሃኒት የተነከሩ አጎበሮችን በመጠቀም ልንከላከል ይገባል ፡፡
    በጋራ ጤናችንን እንጠብቅ!!
    በጋራ የማናልፈውና የማንወጣው ችግር የለም !!!
    የድሬዳዋ አስተዳደር!!!