ክቡር ከንቲባ ከድር ጁሀር ከሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ጋር በመሆን፤ አመሻሹን በ06 ቀበሌ ቀፊራ ገበያ ውስጥ የሚገኙ መንገዶችን ቅኝት አድርገዋል።

    ክቡር ከንቲባ ከድር ጁሀር ከሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ጋር በመሆን፤ አመሻሹን በ06 ቀበሌ ቀፊራ ገበያ ውስጥ የሚገኙ መንገዶችን ቅኝት አድርገዋል። ከዚህ ቀደም በሳምንታዊ የፅዳት ዘመቻ ላይ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት፤ የቀበሌው ፅ/ቤት ከደንብ አስከባሪና ከፀጥታ አካላት ጋር በሠራው የግንዛቤና ህግ የማስከበር ስራ፤ ከመኖሪያ ቤቶች በሚለቀቅ ፍሳሽ ቆሻሻ ምክንያት ይበከሉ የነበሩ የገበያው መንገዶች መሻሻል እንደታየባቸው ተመልክተዋል። ምንጭ፦ከንቲባ ጽ/ቤት

    Read More

      የሀገርን ጥሪ የተቀበሉ ከ200 በላይ የቀድሞ ሰራዊትና ምልስ ሰራዊት አባላት በድሬዳዋ አስተዳደር ሽኝት ተደረገላቸው።

      የሀገርን ጥሪ የተቀበሉ ከ200 በላይ የቀድሞ ሰራዊትና ምልስ ሰራዊት አባላት በድሬዳዋ አስተዳደር ሽኝት ተደረገላቸው። የሽብርተኛውን ቡድን ሀገር የማፍረስ ሴራና የከፈተውን ጦርነት ለማክሸፍ የሚካሄደውን ሀገር የማዳን ጥሪን በመቀበል የቀድሞ ጦር ሰራዊትና የመከላከያ ሰራዊት ምልስ አባላት ዛሬ ሽኝት ተደርጎላቸዋል። በስነስርዓቱ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ባስተላለፉት መልእክት እንዳሉት ዘማቾች ወንጀለኛው ቡድን ሀገሪቱ ላይ የጀመረውን የንጹሀን…

      Read More

        ለ9 ዙር የፅዳት ዘመቻ በዛሬው እለት ተካሂዷል ።

        ለ9 ዙር የፅዳት ዘመቻ በዛሬው እለት ተካሂዷል ። በዛሬው እለት ከጠዋቱ 12:00 ሰአት ጀምሮ ከሰኢዶ እስከ ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም ከድል-ጮራ እስከ ደቻቱ ድረስ ባሉት አካባቢዎች ላይ የፅዳት ዘመቻው የተካሄደ ሲሆን በዚሁም የፅዳት ዘመቻ ላይ ከፍተኛ የአስተዳደሩ አመራሮችና ፣ የሴክተር ተቋማት ሰራተኞችና አመራሮች ፣ የድሬዳዋ ከተማ ስፖርት ክለብ ደጋፊዎች ፣ በበጎ-አድራጎት ስራዎች ላይ የተሰማሩ አካላት ብሎም…

        Read More