የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ አመራርና ባለሙያዋች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ ተወያዩ። በወይይቱም የተቋሙ ሰራተኞች ለመከላከያና ለተፈናቀሉ ወገኖች ድጋፍ አጠናክሮ ለማስቀጠል የቢሮ ድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ አዋቅረዋል። ሁሉም የተቋሙ ሰራተኞች ለመከላከያ ሰራዊት ደጀን በመሆን ሀገራቸውን ከመፍረስ እንደሚታደጉ በአንድ ድምፀ ቃል ገብተዋል።