16ኛው ብሔር ብሔረሰቦች ቀን በዓል የድሬዳዋን መልካም ገጽታ ገንብቶ ያለፈ መሆኑ ተገለፀ

    የበዓሉ አከባበር ሂደት ተገመገመ:-
    በግምገማው :-
    ** ከጸጥታ አንጻር ከአጎራባች ክልሎች ጋር በመሰራቱ በዓሉ በሰላምና ካለምንም የጸጥታ ችግር እንዲጠናቀቅ ማስቻሉ::
    ** እንግዶችን በየደረጃው ከማስተናገድ አንጻር በተሳካ ሁኔታ መፈጸሙ።
    ** ለነዋሪውና ለእንግዶች ተጠቃሚ ያደረገ የሀገር ውስጥ አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርትና አገልግሎታቸውን ለማስተዋወቅ እንደዚሁም ለገበያ ለማቅረብ ያስቻለ ከሀገር ውስጥ ባለፈ የአጎራባች ሀገሮች አምራቾችን ያካተተ የንግድ ትርኢትና ባዛር በተሳካ ሁኔታ መከናወኑን::
    ** ለጀግናው የመከላከያ ሰራዊት የሚውል ደም ለወገኔ በሚል መሪ ቃል ደም የመለገስ ስነስርአት መከናወኑን::
    ** የዜጎች ወንድማማችነትን ከማጎልበት የብሔር ብሔረሰቦች የበለጠ እንዲተዋወቁ እና እንዲተሳሰሩ ሚያስችሉ ስነስርዓቶች መከናወናቸው::
    በአጠቃላይ በዓሉ ድሬዳዋን መልካም ገጽታ ገንብቶ ያለፈ እንደሆነ ለመገምገም ተችሏል፡፡