በአፋር ክልል በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የተገኘ ከ13 ሚሊየን ብር በላይ ተያዘ::
በአፋር ክልል በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የተገኘ ከ13 ሚሊየን ብር በላይ መያዙን የአውሳ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል። ገንዘቡ በኮሪ ወረዳና በጭፍራ ወረዳ በኬላ ላይ በተደረገ ፍተሻ የተገኘ ሲሆን፥ የአውሳ ዞን ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ረዳት ኮሚሽነር አሃዶ መሀመድ እንደገለፁት፥ በክልሉ አውሳ ዞን ሁለት ወረዳዎች ኬላ ላይ በተደረገ ፍተሻ 13 ሚሊየን 53 ሺህ 490 ብር ተይዟል ብለዋል፡፡…


