በድሬዳዋ አስተዳደር የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የእድገት ደረጃ ሽግግር እውቅና መርሀ-ግብር ተካሄደ
በድሬዳዋ አስተዳደርና በፌደራል ትብብር በተፈጠሩ ምቹ ሁኔታዎች የከተማዋን የኢንዱስትሪ ማዕከልነትና በቀዳሚነት የሚያረጋግጡ ኢንዱስትሪዎች እየተስፋፉ ሲሆን በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎች መስፋፋት ከተፈጠሩ ምቹ ሁኔታዎች መካከልም በከተማዋ የተገነቡት የኢንዱስትሪ መንደርና የኢንዱስትሪ ፓርክ ናቸው ፡፡ እነዚህም በመቶዎች የሚቆጠሩ አነስተኛ መካከለኛና ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች የድሬዳዋን የኢንዱስትሪ ማዕከልነት የሚያረጋግጡ ብቻ ሣይሆኑ አልሚዎችና ነዋሪዎቿ ብሩህ ተስፋ የሚያሰንቁ ብሎም ለሀገራችን የኢኮኖሚ ዕድገትም የላቀ አስተዋፆ የሚያበረክቱም…


