በመሆኑም ተጋባዥ እንግዶች፣ መላው የድሬደዋ አመራሮችና ነዋሪዎች በፕሮግራሙ ላይ በመገኘት አሻራዎን እንድያስርፉ ጥሪ ያስተላልፋል።
በነገው እለት (ሐምሌ 22ቀን 2014) በድሬደዋ አስተዳደር አዲሱ ምድር ባቡር ጣቢያ “አሻራችን ለትውልዳችን” በሚል መሪ ቃል ከፍተኛ የፌዴራል እና የክልል አመራሮች የሚሣተፉበት የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ፕሮግራም ለማካሄድ አስፈላጊውን ቅድመ-ዝግጅት ያጠናቀቀ መሆኑን የድሬደዋ አስተዳደር የአረንጓዴ አሻራ ቴክኒክ ኮሚቴ ገልፅዋል።


