በአስተዳደራችን የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርህ ግብር ከተጀመረ ጊዜ አንስቶ በርካታ ተግባራት ሲከናወኑ ቆይቷል። ድሬዳዋ አስተዳደር አሁን እየጣለ ካለው ዝናብ ጋር ተያይዞ ለችግኝ ተከላ መርህ ግብር ምቹ በመሆኑ በአንድ ጀንበር 700 ሺህ ችግኞች የፊታችን እሁድ ነሀሴ 8/ 2014 በከፍተኛ የህብረተሰብ ታሳትፎ ለማከናወን የሚያስችሉ ዝግጅቶች ተጠናቆ ፤ ለ38ቱም የገጠር ቀበሌና 9 የከተማ ቀበሌዎች የችግኝ ማጓጓዝ ስራ ዛሬ በይፋ ተጀምሯል።

    Read More

      የፌደራል ግብርና ሚንስቴር ሚንስትር ክቡር አቶ ዑመር ሁሴን በድሬዳዋ አስተዳደር ያለውን የግብርና ልማት ስራዎችን ጎበኙ።

      የፌደራል ግብርን ሚንስቴር ሚንስትር ክቡር አቶ ዑመር ሁሴን ፣ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጁሃር እንዲሁም የአስተዳደሩ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በገንደሪጌ ገጠር ቀበሌ በአትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ እየተከነወኑ ያሉ ስራዎችን ጎብኝቷል። ክቡር ሚንስትር አቶ ዑመር ሁሴን በጉብኝት ወቅት እንደገለፁት ባዩት ነገር እጅግ ደስተኛ እንደሆኑ እና በአስተዳደሩ በቋሚ ተክሎች ላይ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን በመስመር ወደ ሌሎች…

      Read More

        በድሬዳዋ አስተዳደር በጎዳና ተዳዳሪና አካል ጉዳተኛ ህፃናት ዙሪያ ለመስራት የሚያስችል ፕሮጀክት በዛሬው እለት በይፋ ተጀመረ ።

        ኤስ ኦ ኤስ የህፃናት መንደር ፕሮግራም መንግስታዊ ያልሆነ አለም አቀፋዊ የበጎ አድራጎት ድርጅት ሲሆን በሀገራችን ኢትዮጲያ ወላጆቻቸውን በተለያየ ምክንያት ያጡ ህፃናትን አሰባስቦ ከለላ በመስጠት ራሳቸውን ችለው ሀገራቸውን እንዲያገለግሉ የሚያደርግና የቤተሰብ ማጠናከሪያ ፕሮግራሞችን በመቅረፅ ለቤተሰብና ለማህበረሰብ ተቋማት ድጋፍ በመስጠት ቤተሰብ እንዲጠናከርና ልጆች የመብቶቻቸው ተጠቃሚ ይሆኑ ዘንድ የሚሰራ ተቋም ነው ። ኤስ ኦ ኤስ በድሬዳዋ አስተዳደር ከማርች…

        Read More