“በድሬዳዋ አስተዳደር አሁን ላይ እየተከናወኑ የሚገኙት ግዙፍ ፕሮጀክቶች በሀገር አቀፍ ደረጃም በምሳሌ የሚቀርቡ ናቸው”።

በዛሬው ዕለት በሱማሌ ክልል ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ኢብራሂም ኡስማን የተመራ ልኡካን ቡድን በድሬዳዋ አስተዳደር እየተከናወኑ የሚገኙ ትልልቅ ፕሮጀክቶችን ተዘዋውሮ ጎብኝቷል።

ልኡክ ቡድኑ በጉብኝቱም የድሬዳዋ አስተዳደር ሁለገብ ወጣቶች ማዕከልን፣ የክብር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ ፖርክን፣ ሲቪክ ሴንተርን እንዲሁም የድሬዳዋ ኢንተርናሽናል እስታዲየምን ጎብኝቷል።

በጉብኝቱ ወቅት ያነጋገርናቸው የሱማሌ ብሄራዊ ክልል ም/ ፕሬዝዳንት አቶ ኢብራሂም ኡስማን አሁን ላይ በድሬደዋ አስተዳደር እየተከናወኑ የሚገኙት ግዙፍ ፕሮጀክቶች በሀገር አቀፍ ደረጃም በምሳሌነት የሚቀርቡ ናቸው በማለት ተናግረዋል።

ም/ ፕሬዝዳንቱ አያይዘውም በተሰሩት የፕሮጀክት ስራዎች የአመራሩ ቁርጠኝነት የሚታይ በመሆኑ አመስግነው በዚሁ ይቀጥል በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *