የድሬዳዋ አስተዳደረ የስነ-ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ከአስተዳደሩ ለተውጣጡ የ1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ርዕሳነ መምህራን ለጤና ተቋማት ሀላፊዎች እንዲሁም ለሰው ሀብት ዳይሬክቶሬት ሀላፊዎች በሀብት ማሳወቅና ምዝገባ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠት ጀመረ::
በመድረኩ የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር የስነ-ምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ፌኑስ አብዱልጀባር የስልጠና መድረኩ ዋነኛ አላማ በሀብት ማሳወቅና ምዝገባ ፅንሰ ሀሳብና አተገባበር ላይ ግንዛቤ ለመፍጠር መሆኑን ጠቁመዋል::
ሀብት ማሳወቅና ማስመዝገብ ሙስናና ብልሹ አሠራርን ለመከላከልና መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው የተናገሩት አቶ ፌኑስ ስለ ሀብት ምዝገባና ጠቀሜታም ሰፊ ማብራሪያ ሰተዋል::
በመጨረሻም አቶ ፌኑስ ማንኛውም የመንግስት ሰራተኛና አመራር ሀብቱን በማስመዝገብና በማሳወቅ ሀላፊነቱን መወጣት አለበት ሲሉ ተናግረዋል::


