የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ሴሪል ራማፎሳ ከብሪክስ የብራዚል ጉባዔ ጎን ለጎን ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር መክረዋል።
ፕሬዝዳንቱ በኤክስ ገጻቸው ላይ እንዳሰፈሩት “ሁሌም ወንድሜን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማግኘቴ ደስተኛ ነኝ” ብለዋል።
በብራዚል ሪዮ ዲጄኔሮ በተካሄደው 17ኛው የብሪክስ ጉባኤ፤ የአፍሪካን ፍላጎት እና ሁለንተናዊ ጥቅም ለማሳደግ በትብብር ለመስራት ቁርጠኛ መሆናቸውንም አረጋግጠዋል።


