በኢትዮጵያ የብስክሌት ስፖርት ውድድር ታሪክ ውስጥ በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የጥሎ ማለፍ የታዳጊዎች ውድድር በድሬዳዋ ተከናወነ

የፈናን ፔይ የብስክሌት ሻምፒዮና የጥሎ ማለፍ ጫወታ አንደኛና ሁለተኛ ሆነው ባጠናቀቁት በአቤኔዘር አለሙና እና ኢሳኮር ፍሬው መካከል የታየው ፉክክር በስፍራው ከታደመው የስፖርት አፍቃሪ እና ተመልካች ከፍተኛ አድናቆት ተችሮታል። አርባ ሁለት ዙሮችን በሚሸፍነውና በያንዳንዱ ዙር መጨረሻ የሆነ ተወዳዳሪ ከጫወታ ውጪ እየሆነ የመጨረሻዎቹ ሁለት ተወዳዳሪዎች እስኪቀሩ ድረስ ጠንካራ ፣ አጓጊና ብርቱ ፉክክር በታየበት በዚህ በአራተኛው ቀን የፈናን…

Read More

የኢንደስትሪ ፖርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በክረምት የበጎ ፍቃድ መርሃ-ግብር በድሬዳዋ በአሰሊሶ ክላስተር በሚገኙ ሁለት የገጠር ቀበሌዎች የአረጋውያን የቤት ግንባታን አስጀመረ

በዚህም የኢንደስትሪ ፖርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ፍስሀ ይታገሱ በአሰሊሶ ክላስተር ገደንሰር ገጠር ቀበሌ እንዲሁም በአሰሊሶ ገጠር ቀበሌ የአቅመ ደካሞች የቤት ግንባታን አስጀምረዋል። የኢንደስትሪ ፖርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ፍስሀ ይታገሱ በክረምት የበጎ ፍቃድ ስራዎች አቅመ ደካማ ወገኖችን የማገዝ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልፀው፤ቤቶቹ በ 2 ሚሊየን ብር ወጪ እንደሚገነቡ እና በአንድ…

Read More

ፓስተር ዮሀንስ ኦላና እና ቤተሰቦቹ ከድሬዳዋ አስተዳደር እና ከዲያስፖራ ማህበር ጋር በመተባበር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሄዱ

ፓስተር ዮሀንስ ኦላና እና ቤተሰቦቹ የምስራቅ መካከለኛው አፍሪካ ከሰባተኛው ቀን አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን ዋና የፋይናስ አስተዳዳሪ( CFO) ከድሬዳዋ አስተዳደር እና ከዲያስፖራ ማህበር ጋር በመተባበር የገጠር ሴት ተማሪዎች ሆስቴል ትምህርት ቤት ቅጥር ጊቢ ውስጥ ችግኝ ተክለዋል። በችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ ዳያስፖራ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ቢኒያም ግርማ እንደተናገሩት መንግስት የአየር ንብረት…

Read More

በድሬዳዋ አስተዳደር በአረንጓዴ አሻራ ስራዎች ከሚተከሉት ችግኞች መካከል 85 በመቶ የሚሆኑት ለምግብነት የሚውሉ ፣ ሙቀት የሚቋቋሙ እና የውሃ እጥረት የሚችሉ ናቸው”። ወ/ሮ ፈቲህያ አደን – የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ

“በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ቃል የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ከኢ.ፌ.ዴ.ሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የድሬዳዋ እንደራሴዎች እና በስሩ ካሉ ተጠሪ ተቋማቶች ጋር በጋራ በመሆን የክረምት የበጎ ስራ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃግብርን አከናወኗል። የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፈቲህያ አደን በመርሃግብሩ ላይ እንደተናገሩት ድሬዳዋ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላት ፣ ከፍተኛ የጎርፍ ተጋላጭነት እና…

Read More