“ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር” በሚል መሪ ሀሳብ የብልፅግና ፓርቲ ያለፉት ዓመታት ጉዞና የቀጣይ ዓመታት የትኩረት መስኮች ላይ የሚመክር መድረክ በድሬዳዋ በትላንትናው እለት መካሄድ ጀመረ።

በብልፅግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ለአስተዳደሩ አጠቃላይ አመራሮች የተዘጋጀው የምክክር መድረክ ቃል በተግባር የተገለጠበት የፓርቲው ያለፉት ዓመታት ጉዞ እንዲሁም በቀጣይ ስኬቶችን ለማስቀጠል፣ ክፍተቶችን ለመሙላትና በእቅድ የተያዙ ስራዎችን የሕዝቡን የላቀ ተጠቃሚነት በሚያረጋግጥ መልኩ በውጤታማነት መፈፀም የሚያስችል አቅም መፍጠሪያ መድረክ ነው።

መድረኩ ለተከታታይ አራት ቀናት የሚቆይ ይሆናል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *