በድሬዳዋ እግር ኳስ ፌደሬሽን አዘጋጅነት ሲካሄድ የቆየው የድሬዳዋ ሁለተኛ ዲቪዚዮን ክለቦች ውድድር በሮሃ ቡድን አሸናፊነት ተጠናቋል።
ሮሃ ገበያ ከ አዲጋላ ጋር ለዋንጫ የተጫወተ ሲሆን በሮሃ ቡድን 5-2 አሸናፊነት ነው ጨዋታው የተጠናቀቀው።
በመጀመሪያው አጋማሽ የአዲጋላ ቡድን ሁለት ጎሎችን በማስገባት ቀዳሚ ሆኖ ጨዋታውን እየመራ ቢቆይም የሮሃ ቡድን ባስቆጠረው አንድ ጎል የመጀመሪያውን አጋማሽ ጨዋታ 2-1 በሆነ ውጤት ተጠናቆ፤ ከእረፍት መልስ በሁለተኛው አጋማሽ የሮሃ ቡድን በተከታታይ ባስቆጠራቸው አራት ግቦች 5-2 በሆነ ውጤት ሮሃ ቡድን የዲቪዚዮኑ ሻንፒዮን በመሆን ወደ ከፍተኛ ዲቪዚዮን መዘዋወሩን አረጋግጧል።
ጨዋታውን የተከታተሉት የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ በተለያዩ ዘርፎች ላሸነፉ ተጫዋቾች እና ቡድኖች ሽልማት አበርክተዋል።


