በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አንባሳደር አሌክስ ላሜክ የተመራ ልዑካን ቡድን ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ድሬዳዋ ከተማ ገባ

ልዑኩ ከድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ጋር እንዲሁም ከአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በማህበራዊ ፣ በኢኮኖሚያዊ እና በዲፕሎማሲው መስክ ስራዎችን በተጠናከረ መልኩ መስራት በሚቻልባቸው ነጥቦች ላይ ምክክር የሚያደርግ ይሆናል። ልዑኩ ድሬዳዋ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርስ በድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር፣ በድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ በክብርት ወ/ሮ ፈቲያ አደን፣ በድሬዳዋ አስተዳደር…

Read More

ፈረንሳይ እና ድሬዳዋ በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊ እና በዲፕሎማሲያዊ መስኮች ስራዎችን በጋራ አጠናክረው እንደሚሰሩ አስታወቁ

የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ከአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በጋራ በመሆን በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አንባሳደር አሌክስ ላሜክ ከተመራ ልዑካን ቡድን ጋር በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊ እና በዲፕሎማሲያዊ መስኮች ስራዎችን በጋራ አጠናክሮ ለመስራት በሚቻልባቸው ነጥቦች ላይ ተወያይተዋል። በዚህም በመድረኩ ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ለእንግዶች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸውን በማስተላለፍ፤ ድሬዳዋ ቀንም ለሊትም እንቅስቃሴ ያላት ሰላማዊ ከተማ…

Read More

የሲንጋፖር ሪፐብሊክ ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግን በክብር ተቀብያለው።

ውይይታችን በሁለቱ ሀገሮቻችን መካከል ያለንን ግንኙነት ለጋራ ነጋችን ወሳኝ በሆኑ መስኮች በጋራ ለመሥራት በምናደርገው ጥረት ውስጥ አንድ ጠቃሚ ርምጃ ነው። በተለይም በክሂሎት ልማት እና የካርበን ብድር ትብብር ላይ ያደረግናቸው የመግባቢያ ስምምነቶች ጽኑ እና ለነገው ገበያ ዝግጁ የሆኑ ሠራተኞችን ለማፍራት ብሎም በአየር ንብረት ጥበቃ ረገድ ዘላቂ፣ ዝቅተኛ ካርበን የሚያወጣ እድገት ለማረጋገጥ ያለንን የጋራ አቋም የሚያንፀባርቅ ነው።…

Read More

በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር የሆኑት ክቡር አሌክሲስ ላሜክ፥ ወደ ‘ትንሿ ኢትዮጵያ’ ድሬ በመምጣታቸው ከልብ ደስ ብሎኛል።

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከዚህ ቀደም፥ በኢትዮጵያ ላይ ኢንቨስት እንዲያደርጉ ለፕሬዝዳንት ማክሮን ያቀረቡትን ግብዣ ተከትሎ የተደረገው ይህ የሥራ ጉብኝት፥ ታሪካዊውን የድሬዳዋ እና የፈረንሳይ ግንኙነት በይበልጥ የሚያጠናክር ነው። 16 የኢንቨስትመንት ቡድን አባላትን ከያዘውና በአምባሳደር ላሜክ ከተመራው ልዑክ ጋር በነበረን ቆይታ የእህትትማማች ከተሞችን ግንኙነት ለማሳደግ፥ በባህል እና ቱሪዝም መስኮች ድጋፍ ለማድረግ፥ እንዲሁም የፈረንሳይ ባለሀብቶች በአስተዳደራችን…

Read More

የኢፌዴሪ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር መኩሪያ ኃይሌ የድሬ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ እና የኮሪደር ልማት ግንባታን ጎበኙ

#DGC ህዳር 15/2018 የኢፌዴሪ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር መኩሪያ ኃይሌ በድሬዳዋ አስተዳደር ተገንብቶ በቅርቡ ተመርቆ አገልግሎት እየሰጠ ያለው ድሬ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ እና የኮሪደር ልማቶችን ጎብኝተዋል ። ድሬ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሙስናን ለመከላከልና ብልሹ አሰራሮችን ቀድሞ ከመቆጣጠር አንፃር በቴክኖሎጂ በታገዘ መልኩ የሚከወንና የስራ ባህልን የሚቀይር በመሆኑ በድሬዳዋ የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ መቀጠል…

Read More