የድሬዳዋ አስተዳደር ካቢኔ ዛሬ ከሰአት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ አጀንዳዋች ተወያይቶ ውሳኔ አስተላልፏል።
1ኛ:- የከተማ ወረዳዎች አደረጃጀት ላይ ተወያይቶ አፅድቋል።
2ኛ:- የከተማ መሬት ይዞታ አገልግሎቶች ተመን ማሻሻያ ላይ ካቢኔው ተወያይቷል።
3ኛ:- የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ምክር ቤት ማቋቋሚያ ደንብ ካቢኔው ተወያይቶ ውሳኔ አስተላልፏል።
በመጨረሻ ካቢኔው በመሬት እና መሬት ነክ አጀንዳዎች ላይ በመወያየት ውሳኔዎችን አስተላልፏል።
የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ


