• በኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ዕድገት ውስጥ እንደ አንድ ትልቅ ምዕራፍ የሚጠቀሠው የአርጆ የድንጋይ ከሰል ፋብሪካ ከውጭ የሚገባውን የድንጋይ ከሰል ፍላጎት ለመተካት የሚያግዝ ነው።
• የአርጆ የድንጋይ ከሰል ፋብሪካ በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር በሚገኘው ብሔራዊ ማዕድን ኮርፖሬሽን የሚተዳደር ነው።
• ፋብሪካው ለኢትዮጵያ ዕድገት ወሳኝ ለሆኑት የሲሚንቶ፣ የብረት ብረት እና የማምረቻ ኢንዱስትሪዎች የድንጋይ ከሰል ያቀርባል።
• ፋብሪካው በሰዓት 200 ቶን የማምረት አቅም ያለው ሲሆን 250 ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል የፈጠረ ነው።
• ኬሚካል አልባ አሰራርን በመከተል ለአካባቢ ደህንነት መረጋገጥ አስተዋጽኦም ያደርጋል።
• አንድ ቢሊዮን ብር የሚሆን ገንዘብ ኢንቨስት የተደረገበት ፋብሪካው በአንድ ዓመት ከግማሽ ጊዜ ውስጥ ተገንብቶ የተጠናቀቀ ነው።
• ይህ ፕሮጀክት ኢትዮጵያ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የኢንዱስትሪ ዕድገትን ከአካባቢ ጥበቃ ጋር እንዴት አጣምራ መጓዝ እንደምትችል የሚያሳይ ነው።


