በወለጋ ዞኖች እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች አስደሳች ናቸው – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
በወለጋ ዞኖች እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች ተስፋ ሰጪ እና አስደሳች መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዛሬው ዕለት በቄለም ወለጋ፣ በምዕራብ ወለጋ (ጊምቢ) እና በምስራቅ ወለጋ (ነቀምት) ዞኖች በመዘዋወር የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የወለጋ ሕዝብ ሰላም ወዳድ፣ ሥራ ወዳድ እና በፍቅር የተሞላ መሆኑን ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል። “የወለጋ ሕዝብ ጠላቱ እንኳን ቢሆን…


