የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ እና የንግድ ኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀርቢ ቡህ እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ ብለዋል
ዒድ አል ፈጥር በዓል በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ ልዩ ትርጉም ያለው የቅዱሱ የረመዳን የፆም ወር ማሳረጊያ ታላቅ በዓል ነው፡፡
በዓሉ ሕዝበ ሙስሊሙ በረመዳን ወቅት ሲያደርገው እንደነበረው በአንድነት ተሰባስቦ ያለው ለሌለው በማካፈል ማህበራዊ ትስስሩን ይበልጥ አጠንክሮ በአብሮነት የሚያከብረው በዓል ነው ብለዋል።
በድጋሚ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የብልፅግና፣ የአብሮነት እና የመተሳሰብ እንዲሆን መልካም ምኞቴን ገልፀዋል።
ኢድ ሙባረክ!


