የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋሊያዎቹ) ከሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔን ጋር የደርሶ መልስ ጨዋታ ለማድረግ ድሬዳዋ ከተማ ገቡ

በ36ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋሊያዎቹ) የሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔ አቻቸውን 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት ማሸነፋቸው ይታወቃል።

​ ታዲያ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የደርሶ መልስ ጨዋታውን ከሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔ አቻቸው ጋር በድሬዳዋ አለም አቀፍ ስታዲየም ለማድረግ ነው ድሬዳዋ ከተማ የገባው።

ልዑኩ ድሬዳዋ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ሲደርስ በድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገበየሁ ጥላሁን፣ በድሬዳዋ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ኮምሽን ኮምሽነር አቶ ካሊድ መሀመድ፣ በካቢኔ አባላት እንዲሁም በአስተዳደሩ በየደረጃው በሚገኙ አመራሮች ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል።

ጨዋታው የፊታችን ማክሰኞ መጋቢት 22/2018 ዓ.ም የሚካሄድ ይሆናል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *