ቀፊራ፦ የታሪክና የዘመናዊነት ውህደት!

​የድሬዳዋ የንግድ ምልክት እና የታሪክ መዘክር የሆነው ታሪካዊው የቀፊራ የገበያ ማዕከል፣ በኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ተገቢውን ትኩረት አግኝቶ በዘመናዊ መልኩ ታድሶ ዛሬ በይፋ ተመረቀ።

​ከ1939 ዓ.ም ጀምሮ የንግድና የባህል ማዕከል ሆኖ የቆየው ይህ ስፍራ፣ የነበረበትን የጽዳትና የትራፊክ መጨናነቅ ችግር በመቅረፍ ለከተማዋ አዲስ ድምቀት ሆኗል።

​ የማዕከሉ ጥንታዊ የህንጻ ጥበብ እና ታሪካዊ ቅስቶች (Arches) ሳይቀየሩ ጸንተው እንዲቆዩ ተደርጓል።

​ነጋዴዎችን ከጸሐይና ከዝናብ የሚከላከሉ ዘመናዊ መጠለያዎች (Sheds) እና የውሃ ፍሳሽ ማስወገጃዎች ተገንብተውለታል።

​ማዕከሉ በዘመናዊ መብራቶች በመደምቁ ለምሽት ግብይትና ለደህንነት ምቹ ሆኗል።

​ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር እንደገለጹት፤ ቀፊራ ለድሬዳዋ ብቻ ሳይሆን ለጎረቤት ሀረርጌ፣ ለሶማሌ ክልልና እስከ ጅቡቲ ድረስ ምርት የሚያከፋፍል የንግድ ዋልታ ነው።

​የብልፅግና ፓርቲ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ በበኩላቸው፤ “የእናት ጓዳ” የተባለለትን ይህን ስፍራ ከነበረበት የተዘበራረቀ አሰራር ማውጣት መቻሉን ገልጸዋል።

​ማዕከሉ ከንግድ ባለፈ የከተማዋ ትልቅ የቱሪዝም ሀብት ሆኖ እንዲያገለግል በትኩረት እንደሚሰራም ተጠቁሟል።

​የቀድሞ ግርማ ሞገሱን ከዘመናዊ አሰራር ጋር ያዋሃደው የቀፊራ ገበያ ለነጋዴዎችም ሆነ ለሸማቾች እንኳን ደስ አላችሁ!

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *