ያለ እድሜ ጋብቻን፣ የሴት ልጅ ግርዛትን እና ሌሎች ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ለማስቆም የተዘጋጀውን ፍኖተ ካርታ (Road Map) ከአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ግንዛቤ ለማስጨበጥ እና የመግባቢያ ሰነድ ለመፈራረም የተዘጋጀ መድረክ ተካሄደ። በመድረኩ የአስተዳደሩ ከፍተኛ የፓርቲ አመራሮች፣ የምክር ቤት አመራሮች እና የካቢኔ አባላት ተገኝተዋል።