በድሬ ፔትሮሊየም ካምፓኒ በ10 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባው የነዳጅ ማደያ ስራ ጀመረ::
የድሬደዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አህመድ መሀመድ ቡህ እና ሌሎች የመንግስት የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት የተመረቀው ይህ የነዳጅ ማደያ በቀን 250 ሺህ ሊትር ነዳጅ የመያዝ አቅም ያለው ሲሆን ለ24 ሰዓታት ያለማቋረጥ አገልግሎት ለመስጠት መዘጋጀቱን የድሬ ፔትሮሊየም ካምፓኒ ተወካይ የሆኑት አቶ አለማየሁ ደነቀ ተናግረዋል፡፡ካምፓኒው ለምስራቅ ሀረርጌ ያለውን የነዳጅ ችግር በሚችለው አቅሙ ለመቅረፍ እንደሚሰራ ተወካዩ ገልጸዋል፡፡ በተለይ አሁን ላይ…


