በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ለ6ኛው አገርአቀፍ ጠቅላላ ምርጫ ህጋዊ እውቅና አግኝተው የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፖርቲዎች የጋራ መድረክ ምስረታ አካሂደዋል ።

    በመድረኩ ዘጠኝ ፖርቲዎች የተሳተፈ ሲሆን የጋራ መግባቢያ የቃል ኪዳን ሰነድ ተፈራርመዋል።
    የፖለቲካ ፖርቲዎች መካከል የጋራ መድረክ መመስረቱ:-
    *በተፎካካሪ ፖርቲዎች መካከል በመተማመን ላይ የተመሰረተ ዲሞክራሲያዊ ውይይት እንዲኖ ለማስቻል ።
    *በመደማመጥና በመከባበር ላይ የተመሰረተ ምክንያታዊ ውይይት እንዲኖር።
    *የአገራዊ ጥቅምን ቅድሚያ መስጠትን።
    *የህዝብን ጥቅም ማስቀደም።
    *መሰረታዊ የሆኑ የሰብዓዊና የእኩልነት መርሆዎችን የተከተለ የጋራ የምክክር መድረክ በዘላቂነት እንዲኖር ለማስቻል ።
    *በቀጣይ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ለማካሄድ ።
    ***የፖለቲካ ፖርቲዎች የሚዲያ አጠቃቀምን ህግንና ስርአትን የተከተለ ለማድረግ ።
    ባጠቃላይ ምርጫና ምርጫ ነክ የሆኑ ጉዳዬችን በሰላማዊ መንገድ ለማከናወን የፖለቲካ ፖርቲዎች የጋራ መድረኩ መመስረቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው በምስረታና የቃል ኪዳን ሰነድ መፈራረሚያ ስነስርአቱ ላይ ተገልጿል።