በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ለ6ኛው አገርአቀፍ ጠቅላላ ምርጫ ህጋዊ እውቅና አግኝተው የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፖርቲዎች የጋራ መድረክ ምስረታ አካሂደዋል ።
በመድረኩ ዘጠኝ ፖርቲዎች የተሳተፈ ሲሆን የጋራ መግባቢያ የቃል ኪዳን ሰነድ ተፈራርመዋል። የፖለቲካ ፖርቲዎች መካከል የጋራ መድረክ መመስረቱ:- *በተፎካካሪ ፖርቲዎች መካከል በመተማመን ላይ የተመሰረተ ዲሞክራሲያዊ ውይይት እንዲኖ ለማስቻል ። *በመደማመጥና በመከባበር ላይ የተመሰረተ ምክንያታዊ ውይይት እንዲኖር። *የአገራዊ ጥቅምን ቅድሚያ መስጠትን። *የህዝብን ጥቅም ማስቀደም። *መሰረታዊ የሆኑ የሰብዓዊና የእኩልነት መርሆዎችን የተከተለ የጋራ የምክክር መድረክ በዘላቂነት እንዲኖር ለማስቻል ።…


