በቀስቀሳ ላይ ፖርቲው በማህበራዊ ÷ በኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዘርፍ በቀጣይ የሚያከናውናቸው እቅዶች ገለፃ የተደረገ ሲሆን በዋናነት ከነዋሪው የሚነሱ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት እንደሚንቀሳቀስ ተገልጿል።
በፖርቲው ስር አዋሌቀበሌን ወክለው ለድሬደዋ ምክርቤት የሚወዳደሩ ሶስት እጩዎችን ማለትም:-
* አቶ ኑረዲን መሀመድ
*ወ/ሮ ሳኒያ ሙስጠፋ
*አቶ ሙራድ ሙክታር
ለቀበሌው ነዋሪዎች አስተዋውቋል
በተጨማሪ አቶ ኑረዲን መሀመድ እንዳሉት ፖርቲያችን ብልፅግናን ከመረጣቹ በቀበሌ ና በአስተዳደሩ የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት ጠንክረን እንሰራለን ቡለል ።
በቀበሌው አራት ሺ ሁለት መቶ ሰላሳ ሁለት ነዋሪዎች የምርጫ ካርድ መውሰዳቸው ታውቋል።


