በግምገማ መድረኩ የአስተዳደሩ ም/ከንቲባ አቶ አህመድ ቡህ፣የአስተዳደሩ ም/ከንቲባና የንግድ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ሃላፊ አቶ ከዲር ጆሀር፣የፍትህ ፀጥታና ህግ ጉዳዬች ቢሮ ሃላፊ አቶ ሙሳ ጠሐ፣የደሬዳዋ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አለሙ መገራን ጨምሮ ከፍተኛ የአስተዳደሩና የፌደራል የፀጥታና የፍትህ ተቋማት የስራ ሃላፊዎች የተገኙ ሲሆን በተጨማሪም በከተማችን በምርጫው ተሳታፊ የነበሩ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዬች፣የሃይማኖት ተቋማት ተወካዬች፣የአገር ሽማግሌዎች እና ሌሎች የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካለት ተገኝተዋል፡፡
መድረኩን የመሩት የአስተዳደሩ ም/ከንቲባ አቶ አህመድ ብህ እንደገለፁት 6ኛው አገራዊ ምርጫ ህዝቡና ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በጠንካራ ዲስፕሊን እና በጥሩስነ-ምግባር የተሳተፉበት፣የከተማችን ፖሊስና የፀጥታ ዘርፍ ከፌደራል የፀጥታ አካላት ጋር ቅንጅት በመፍጠር ጠንካራ ስራ መስራት በመቻላቸው ምርጫው እጅግ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መነገድ እንዲጠናቀቅ ማድረግ የቻለ ከመሆኑም በላይ እንደ አገርም በአጠቃላይ ኢትዬጲያ ያሸነፈችበት ነው በማለት የገለፁ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር የተጀመረው መልካም ግንኙነት በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል፡፡
በመቀጠልም የፍትህ ፀጥታና ህግ ጉዳዬች ቢሮ ሃላፊ የሆኑት አቶ ሙሳ ጠሐ የአስተዳደሩ ፍትህ ፀጥታና ህግ ጉዳዬች ቢሮ 6ኛው አገራዊ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ ቢሮው በከተማና በገጠር ከፍተኛ ዝግጅት ማደረጉን ገለፀው ምርጫው በሰላማዊ መነገድ በመጠናቀቁም ተሳታፊዎችን እንኳን ደስ አላችሁ በማለት የተናገሩ ሲሆን ከዚህ ቦኃላም አገር ከፓርቲዎችም ሆነ ከምርጫ የምትበልጥ መሆኑን አስገንዝበው የሰላም ምክር ቤቱ በቀጣይም ተጠናክሮ የከተማችንን ሰላም በአስተማማኝ ደረጃ ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ከፍተኛ ሚኖ የሚኖረው መሆኑን በማንሳት በአጠቃላይ በከተማችን ምርጫው እጅግ ሰላማዊና አስደሳች በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ የተወጡ አካላትን አመስግነዋል፡፡
ይህ አስደሳች ውጤት እንዲሁ የተገኘ እንዳልሆነ የገለፁት የመድረኩ ተሳታፊዎች የአስተዳደሩ ፍትህ ፀጥታና ህግ ጉዳዬች ቢሮ፣የድሬዳዋፖሊስ፣ፌደራልፖሊስ እንዲሁም መከላከያ ከዚህ በፊት የነበሩ ክፍተቶችን በማረምና ጠንካራ ቅንጅታዊ አሰራር በፍጠር ከዝግጅት ጀምሮ የሰሩት ስራ ለዚህ ውጤት ከፍተኛ አስተዋፆ ኦያበረከተ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ የድሬደዋ ህዝብ በተለይም በከተማ ናበገጠር የሚኖሩ ወጣቶች ከፀጥታ ሃይሉ ጎን በመሆን ለሰሩት ስራ ሊመሰገኑ እንደሚገባም ገልፀዋአል፡፡
በመድረኩ የተገኙ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ምርጫው እጅግ በጣም ሰላማዊና ፍትሐዊ መሆኑን ገልፀው በዕለቱም ታዛቢዎቻቸውን በተለያዩ ምርጫ ጣቢያዎች አሰማርተው ያለምንም ተፅዕኖ መንቀሳቀሳቸውን ገልፀው ይህሁኔታ በቀጣይም ከዚህ በተሻለ መልኩ እንዲቀጥል ያላቸውን ፍላጎት ገልፀዋል፡፡


