የድሬዳዋ አስተዳደር መንግስት ኮሙዪኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1442ኛው ዓመተ-ሒጅራ ለሚከበረው የኢድ አልአድሃ (አረፋ) በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልፃል ::
በዓሉ በታላቁ የህዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የውሃ ሙሌት በተጠናቀቀበት ማግስት የሚከበር በመሆኑ በዓሉን ደማቅና ልዩ ያደርገዋል ::
የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፉ አቶ እስቅያስ ታፈሰ የሁለተኛው ዙር የህዳሴው ግድብ በመጠናቀቁ መላው የኢትዮጵያ ህዝቦች እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል። መልካም የኢድ አልአድሃ (አረፋ) በዓል እንዲሆንላችሁ በድጋሚ መልካም ምኞታቸውን ተመኝተዋል::
ቀን 12/11/2013 ዓ.ም


