በመሰረታዊ የሸቀጥ ምርቶች ላይ ኢኮኖሚያዊ ምክንያት የሌለው የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ ህገ-ወጥ ነጋዴዎችና ሸማች ማህበራት ላይ የዋጋ ክትትልና ቁጥጥር ግብረ-ሀይል በማቋቋም እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ምክትል ከንቲባና የንግድ ኢንዱሰትሪና ኢንቨሰትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ ከድር ጁሀር አስታወቁ፡፡

    ምክትል ከንቲባ ከድር ጁሀር ከአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች፣ ከፖሊስ ኮሚሽን ኮምሽነር ፣ ከብልፅግና ፓርቲ ፣ከፌደራል አቃቢ ህግ፣ ከገቢዎችና ጉምሩክ ፣ ከዘጠኙ የከተማ ቀበሌዎች ስራ አስፈፃሚዎች
    ጋር በጉዳዩ ላይ ውይይት አድርገዋል።
    ምክትል ከንቲባው በከተማው የመሰረታዊ ፍላጎት እቃዎች ላይ ያለምንም ኢኮኖሚያዊ ምክንያት ዋጋ በሚጨምሩ ፣ምርት በሚያሸሹና በሚያከማቹ ህገ-ወጥ ነጋዴዎችና የሸማች ማህበራት ላይ የተጀመረው አስተዳደራዊና ህጋዊ እርምጃ የመውሰድ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በውይይቱ ወቅት ተናግረዋል፡፡
    እስከአሁን በተወሰደው እርምጃ ከ235 በላይ ሱቆችና መጋዘኖች መታሸጋቸውንና 6 ኤፍሲአር የጭነት መኪኖች ተይዘው ምርመራ እየተጣራ እንደሚገኝም መገለፁን ንግድ ኢንዱሰትሪና ኢንቨሰትመንት ቢሮ በማህበራዊ ትስስር ገፁ ያወጣው መረጃ ያመለክታል።
    ሐምሌ 28/2013 ዓ.ም.