በአስተዳደሩ የተጠቃለለ የ2014 ዓ/ም የካፒታል ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያ ዕቅድ የአስተዳደሩ ከንቲባ ክቡር አቶ ከዲር ጁሃር ከአስፈጻሚ ተቋማት ጋር የቃል ኪዳን ሰነድ የፊርማ ስነ-ስርዓት ተካሄዷል፡፡

    በድሬዳዋ አስተዳደር የሚፈጸሙ የካፒታል ፕሮጀክቶች ነባርና በዚህ ዓመት መጠናቀቅ ያለባቸው ፕሮጀክቶች ቅድሚያ ተሰጥቶአቸው እንደሚሰሩ ነው የአስተዳደሩ ከንቲባ አቶ ከዲር ጁሃር የተናገሩት፡፡
    የካፒታል ፕሮጀክቶቹ እቅድ በአስተዳደሩ ገንዝብና ኢኮኖሚ ቢሮና ፕሮጀክቶቹን በሚያስፈጽሙ ተቋማት በጋራ ተዘጋጅቶ በዛሬው ቀን የፊርማ ስነ-ስርዓት የተቋማት ኃላፊዎች እና ክቡር ከንቲባው ተፈራርመዋል፡፡