ለድሬዳዋ ነዋሪዋች ከአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጆሀር በከፌስ ቡክ ገፃቸው ያስተላለፉት መልዕክት።

    በአስተዳደራችን የሚከበረው 16ኛውን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል፤ መላው የድሬዳዋ ነዋሪዎች፤ የአገራችንን በርካታ ውብ ዕሴቶች በአግባቡ እንድናውቅ፤ በወንድማማችነት መንፈስ ኢትዮጵያዊ ህብረታችንን ይበልጥ እንድናጎለብት፤ እንዲሁም… የእኛ የድሬዳዋውያን መገለጫ የሆነውን፤ በፍቅር እንግዳ የመቀበል መልካም ዕሴታችንን ይበልጥ እንድናጠናክር መልካም አጋጣሚ ይፈጥርልናል። በትውልዶች ታሪክ የማይረሳ አስነዋሪ ድርጊት የፈፀመው አሸባሪው የህወሓት አረመኔ ቡድን፤ በኢትዮጵያውያን ብርቱ ክንድ ግብዓተ መሬቱ እየተፈፀመ…

    Read More

      መላው የድሬደዋ አስተዳደር ነዋሪዎች እና ተቋማት እንዲሁም ድርጅቶች በሙሉ ህዳር 29/2014 ‹‹ወንድማማችነት ለህብረ ብሄራዊ አንድነት›› በሚል መሪ ቃል ለ16ኛ ጊዜ በአስተዳደራችን በሚከበረው የብሄር ብሄረሰቦች ቀን በዓል የድሬደዋ እሴት የሆነውን የፍቅር የአብሮነትና የመቻቻል ባህላችንን ወደ ድሬዳዋ ለሚመጡ እንግዶች በፍጹም ወንድማማችነትና ስሜት በመቀበል ከተማችን የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች በወንድማማችነትና በፍቅር የሚኖሩባት ትንሿ ኢትዮጵያ መሆኑኗን እንድታሳዩና በዓሉ የተሳካ እንዲሆን የበኩላችሁን ሁሉ እንድታደደርጉ በአክብሮት እንጠይቃለን ፡፡ ለበአሉ ድምቀትም ሁሉም ነዋሪና ተቋማት እንዲሁም ድርጅቶች የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ በየበራፋቸሁ እንዲሰቅሉ አስተዳደሩ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡

      Read More

        16 ተኛው የብሄር ብሄረሰቦች ቀን በአል በድሬዳዋ አስተዳደር አዘጋጅነት የፊታችን ህዳር 29 ይካሄዳል ። ከዚሁም በአል ጋር ተያይዞ በአሉን በታላቅ ድምቀት ለማክበር ብሎም ለበአሉ ወደ ከተማችን ድሬዳዋ የሚመጡ እግዶችን ለመቀበል ይቻል ዘንድ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ ።

        በአሉን ተከትሎ በድሬዳዋ አስተዳደር ያለውን የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ፣ ታሪካዊ ቦታዎች እንዲሁም የከተማዋን ኢኮኖሚያ እድገት የሚያበለፅጉ የልማት ስራዎችን ከተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች የመጡ ሀገር አቀፍ የሚዲያ አባላት ጉብኝት አካሂደዋል ። በሀገር አቀፍ ሚዲያ ባለሙያዎች ከተጎበኙ የልማት ድርጅቶች መካከል ለኢኮኖሚው እድገት አይነተኛ አስተዋፆ እየተወጣ የሚገኘው ሸሙ ፋብሪካ ይገኝበታል ። ሸሙ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በ 1999 ዓ.ም…

        Read More

          የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ አመራርና ባለሙያዋች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ ተወያዩ። በወይይቱም የተቋሙ ሰራተኞች ለመከላከያና ለተፈናቀሉ ወገኖች ድጋፍ አጠናክሮ ለማስቀጠል የቢሮ ድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ አዋቅረዋል። ሁሉም የተቋሙ ሰራተኞች ለመከላከያ ሰራዊት ደጀን በመሆን ሀገራቸውን ከመፍረስ እንደሚታደጉ በአንድ ድምፀ ቃል ገብተዋል።

          Read More

            16ኛውን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ምክኒያት በማድረግ ሚዲያ ጉብኝት ተደረገ፣

            16ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል በፌዴሬሽን ምክር ቤት አስተባባሪነት በድሬዳዋ አስተዳደር አስተናጋጅነት “ወንድማማችነት ለሕብረ ብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ሃሳብ እየተከበረ ነው ። የበዓሉ አንዱ አካል የሆነው የአስተናጋጇ የድሬዳዋ አስተዳደር ታሪካዊ ስፈራና የልማታዊ እንቅስቃሴዎች በሚዲያ ባለሙያዎች ጉብኝት ተደረጓል። በጉብኝቱም መርሃግብር በፋሽስቱ ጣልያን ወረራ ጌዜ ከአርበኞች ጋር በመሰለፍ የተሰውትን የአፍሪካዊያን ወንድሞቻችን መካነ መቃብር ጉብኝተዋል። ዓላማውም አፍሪካውያን…

            Read More

              በድሬዳዋ የሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት መግለጫ አውጥቷል ።

              በድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሀገራችን ኢትዮጲያ አሁን ላይ ያለችበትን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ ውይይት በማካሄድ የጋራ መግለጫ አውጥተዋል ። በተለይም የፖለቲካ ፓርቲዎች ከሀገርና ከህዝብ በላይ የሚያስቀድመው አጀንዳ ሊኖር ስለማይችል አሸባሪው የወያኔ ቡድንና ተላላኪዎች እየፈፀሙ ያለውን እኩይ ድርጊት አውግዘው ከህዝባቸውና ከመሪያቸው ጎን እንደሚቆሙም ገልፀዋል ። ውድ ህይወቱን ሳይሰስት በግንባር ለሚፋለመው የመከላከያ ሰራዊትና የፀጥታ…

              Read More

                የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ የብሄር ብሄረሰቦች ቀን የእንኳን አደረሳቹ መልእክት አስተላለፉ

                የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ፈቲህያ አደን ለ16ኛ ጊዜ #ወንድማማችነት ለህብረብሄራዊ አንድነት$ በሚል መሪ ቃል በድሬዳዋ አስተናጋጅነት ለሚከበረው የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን ለመላው ኢትዮጵያዊያን የእንኳን አደረሳቹ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ ክብርት አፈ-ጉባኤዋ በመልእክታቸውም ዘንድሮ ለ16ኛ ጊዜ በውቢቷና የኢትዮጵ ብሄር ብሄረሰቦች በወንድማማችነትና በፍቅር በሚኖሩባት ትንሿ ኢትዮጵያ ድሬዳዋ መከበሩ ልዩ የሚደርገው ለዘመናት የኢትጵያ ብሄር ብሄረሰቦች ሲጠይቁ…

                Read More