የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም በዚህ ዓመት እንደሚተገበር ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ገለጹ

አጠቃላይ የሲቪል ሰርቪሱን ለማዘመን እና የሚፈለገውን ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ያለመው የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም በዚህ ዓመት ተግባራዊ መደረግ እንደሚጀምር ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ አስታውቀዋል።

የዚህ ሪፎርም ዋና ዓላማ የሥራ ፈጠራ እና ተወዳዳሪነት ባህል ማድረግ እንደሆነ የገልጹት ፕሬዚዳንቱ፤ ቀጣሪ መንግሥት ነው የሚለውን የተሳሳተ አስተሳሰብ በማስቀረት አገልግሎት እና ፈጠራን ማዕከል ወደአደረገ ተወዳዳሪነት ለመለወጥ መሆኑ ጠቁመዋል።

የመንግስት ተቋማት ሃሳብን፣ ፈጠራንና ምርታማነት ላይ ትኩረት አድርገው ለውጥ እንዲያመጡ ይጠበቃል ብለዋል ፕሬዚዳንቱ።

በመንግሥት ተቋማት በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ አገለግሎትን ለመስጠትም ሁለንተናዊ ድጋፍ እንደሚደረግ ጠቁመዋል።

EBC

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *