የድሬዳዋ አስተዳደር በሀገር አቀፍ ደረጃ የእውቅና ሽልማት ተበረከተለት ።

” በጎነት ለኢትዮጲያ ከፍታ ” በሚል መሪ ሀሳብ በሀገር አቀፍ ደረጃ የ 2016 የክረምት ወራት የበጎ ፍቃድ ማጠቃለያ መርሀ-ግብር በኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን በዛሬው እለት ተካሂዷል ።

ባሳለፍነው አመት የክረምት ወራት የበጎ-ፍቃድ አገልግሎት በ 14 የተለያዩ መርሀ ግብሮች መከናወኑ ይታወቃል ። ከነዚህም 14 መርሀ-ግብሮች ውስጥም እንደ ድሬዳዋ አስተዳደር ሁሉንም መርሀ-ግብሮች ከማከናወን በዘለለ በሀገር አቀፍ ደረጃ ተሞክሮ የሚሆን የድሬዳዋ አስተዳደር ወጣቶች እና ስፖርት ኮሚሽን የራሳቸውን ሶፍትዌር በማልማት በሀገር አቀፍ ደረጃ አንደኛ በመውጣት ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የፕላቲኒየም ተሸላሚም ሆኗል ።

በኦሮሚያ ክልል በጅማ ዞን በተካሄደው የማጠቃለያ መርሀ-ግብር ላይም የድሬዳዋ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን የወጣቶች በጎ ፍቃድ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ባሃር አብደላ በመገኘት ለአስተዳደሩ የተበረከቱትን የተለያዩ ሽልማቶችን መቀበልም ችለዋል ።

+3

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *