የኮሪደር ልማት በዋናነት የዋና ዋና መንገዶች አካባቢን የማልማት እንዲሁም ፅዱና ውብ የማድረግ ስራ የሚሰራበት ፕሮጀክት መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ ተናገሩ

በድሬደዋ አስተዳደር የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ዓላማና አስፈላጊነት ዙሪያ ከወረዳ 02፣ ከ03 እና 04 ነዋሪዎች ጋር ውይይት ተደርጓል፡፡ በመድረኩ የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ የድሬደዋን ብልፅግናና ዘመናዊ ከተማነት በላቀ መልኩ ለማስቀጠል በርካታ የልማት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን የተናገሩ ሲሆን የኮሪደር ልማት በዋናነት የዋና ዋና መንገዶች አካባቢን ማልማት እንዲሁም ፅዱና ውብ የማድረግ ስራ የሚሰራበት…

Read More

ከሰኞ ነሀሴ 6/2016 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ ሰባት ቀናት የሚቆይ የምክክር እና የአጀንዳ ማሰባሰብ መድረክ እንደሚካሄዱ ተገለፀ

የኢትዮጲያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሰኞ ነሀሴ 6/2016 እስከ ነሀሴ 12/2016 ጀምሮ በድሬዳዋ አስተዳደር የምክክር እንዲሁም የአጀንዳ ማሰባሰብ መድረክ የሚያካሄድ ሲሆን ይህንንም አስመልክቶ የኢትዮጲያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር መሀመድ ድሪር በዛሬው እለት ለሚዲያ አካላት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰተዋል ። በድሬዳዋ አስተዳደር ከፊታችን ሰኞ አንስቶ በሚካሄደው የምክክር እና የአጀንዳ ማሰባሰብ መድረክ ላይም የወረዳ የህብረተሰብ ክፍል ተወካዮች ፣…

Read More

የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ዛሬ ወቅታዊ ጉዳዮችን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ምክንያት ምንም ዓይነት የዋጋ ጭማሪ ለማድረግ የሚያስችል ሁኔታ የለም ብለዋል።

ሚኒስትሩ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን በተመለከተ በመግለጫቸው ካነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች መካከል ተከታዩቹ ይገኙበታል። ማሻሻያው የሀገር በቀል ኢኮኖሚ የሁለተኛው መካከለኛ ዘመን መርሃ ግብር ምሰሶ የሆኑ አራቱን መሰረታዊ ጉዳዮች ማለትም፦ 1) በሀገሪቱ የተረጋጋ ማክሮ ኢኮኖሚ ሁኔታን መፍጠር 2) የንግድ ስራዎችን የሚያሳልጡ የሚያቃልሉና ውጤታማነትን የሚያሻሽሉ የንግድና ኢንቨስትመንት ከባቢን ማሻሻል 3) የዘርፎቹች ምርታማነትና ተወዳዳሪነትን የማሳደግ እና የመንግስት የማስፈጸም አቅምን…

Read More

ኢትዮጵያ በታምራት ቶላ አማካይነት የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች

በ33ኛው የፓሪስ ኦሎምፒክ ዛሬ በተካሄደው የወንዶች የማራቶን ውድድር አትሌት ታምራት ቶላ 1ኛ በመውጣት ለሀገሩ የወርቅ ሜዳሊያ አስገኝቷል። ከ2 ዓመታት በፊት በአሜሪካ ኢዩጂን በተደረገው የዓለም ሻምፒዮና የርቀቱ አሸናፊ የነበረው ታምራት፤ ከ21 ኪሎ ሜትር ጀምሮ ውድድሩን በልዩነት እየመራ በማጠናቀቅ ነው የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት የሆነው።

Read More

የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሀ-ግብር በአስተዳደሩ በስፋት እየተተገበረ መሆኑ ተገለፀ

በድሬዳዋ አስተዳደር ሴቶች ሊግ አስተባባሪነት የሴቶች ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ እንዲሁም የሴቶች አደረጃጀት በጋራ በመሆን የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሀ-ግብር በዛሬው እለት በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሪፈራል ሆስፒታል ቅጥር ጊቢ ውስጥ አከናውነዋል በዚሁ መርሀ-ግብር ላይም በመገኘት ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ክብርት ወ\ሮ ፈቲህያ አደን በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የተጀመረው የአረንጓዴ…

Read More

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ምክኒያት በማድረግ የገበያ ዋጋን ያለአግባብ በሚጨምሩ ህገወጥ ነጋዴዎች ላይ እየተወሰዱ የሚገኙ ህጋዊ እርምጃዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለጸ

የድሬዳዋ አስተዳደር ንግድ እና ኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት ቢሮ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ምክኒያት በማድረግ የገበያ ዋጋን ያለአግባብ በሚጨምሩ እና የኮትሮባንድ ንግድን በሚያካሂዱ ነጋዴዎች ላይ እየተወሰዱ የሚገኙ ህጋዊ እርምጃዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለጸ። የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ እና ንግድ እና ኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት ቢሮ ሀላፊ ክቡር አቶ ሀርቢ ቡህ መንግስት የኢትዮጵያን የምጣኔ ሀብት እድገት በተሟላ መልኩ ለማስቀጠልም አሁን ላይ የማክሮ…

Read More

Imaammataafi Tarsimoo Nyaataafi Sirna Nyaataa Hojiirra Oolchuuf Qophiin Taasifamuun Ibsame.

Biiroon Fayyaa Bulchinsa Dirree Dhawaa Mana Marii Nyaataafi Sirna Nyaataa Sadarkaa Bulchinsaa, Aanaafi Araddaatti Hundeessuuf Sanada Qophaa’erratti Kaabinee Bulchinsaa Waliin Marii Gaggeesse. Imaammanni Nyaataafi Sirna Nyaataafi guutuu biyyaatti akka hojiirra ooluu Itiyoophoyaan waliigaltee “Seqota Declaration” kan mallatteessite yommuu ta’u, Sadarkaa Federaalaarraa jalqabee hanga Araddaatyi Manni Marii hundaa’uudhaan hojiirra oolmaasaafis tarsiimoon qophaa’ee jiraachuu sandni qophaa’ee jiraachuu…

Read More

በድሬዳዋ አስተዳደር የምግብ ስርዓትና የኒውትሪሽን ካውንስል ተቋቋመ

በድሬዳዋ አስተዳደር የምግብ ስርአትና የኒውትሪሽን ረቂቅ ደንብን በዛሬው ዕለት ለካቢኔ ምክር ቤት ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን የድሬዳዋ አስተዳደር የስርአተ ምግብና የኒውትሪሽን ካውንስልም ተቋቁሟል፡፡ በመድረኩ የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር በቀጣይ የካውንስሉን ስራ በተጠናከረ መልኩ መስራት እንደሚገባ የተናገሩ ሲሆን፤ ከምግብ ስርአት ጋር እንዲሁም ከኒውትሪሽን ጋር ተያይዞ በሁሉም ሴክተር ተቋማት ፎካል ፐርሰኖች / ባለሞያዎች/ ተመርጠው…

Read More

የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሀር ለረጅም ጊዜ አስተዳደሩን በማገልገል ባለውለታ ለሆኑት ለአቶ ጣሰው በዳዳ እወቅና ሰጡ

የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት በአስተዳደሩ ለረጀም ጊዜ በቀድሞ ማዘጋጃ ቤት በከተማው የደረቅ ቆሻሻ በማሰባሰብ እና በማስወገድ በባለቢጫዋ ማርቼዲስ መኪና የትራንስፖርት አገልግሎት ሲሰጡ ለነበሩት ለአቶ ጣሰው በዳዳ የአውቅና የምስጋና መርሀ ግብር በማዘጋጀት የዋናጫ እና የ100ሺ ብር የማበረታቻ ሽልማት ከድሬደዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ ከድር ጁሀር እጅ በዛሬው እለት ተበርክቶላቸዋል፡፡ አቶ ጣሰው በዳዳ በድሬዳዋ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ወይም…

Read More