October 2025
ይህ ዘመን በታሪካችን ውስጥ በጉልህ የሚነሳ ነው፡- ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ
ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና በፌዴሬሽን ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ ይህ ዘመን በታሪካችን ውስጥ በጉልህ የሚነሳ ነው ሲሉ ገልጸዋል። እኛ ኢትዮጵያውያን ለበርካታ ዘመናት ስንቆጭባቸው የነበሩትን ታላላቅ ፕሮጀክቶች ያስመረቅንበት ልዩ ዓመት አሳልፈናል ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ የትውልዱ ቁጭት የነበረውን የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አጠናቀን ታሪክ ሰርተናል ብለዋል። በመስከረም ወር…
የዲፕሎማሲያችን ማጠንጠኛው ብሔራዊ ጥቅም እና የዜጎች ክብር ነው፦ ፕሬዚዳንት ታየ አፅቀ ሥላሴ
ፕሬዚዳንት ታየ አፅቀ ሥላሴ በሁለቱ ምክር ቤቶች የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር፤ የዲፕሎማሲያችን መሰረታዊ ማዕከል እና ማጠንጠኛው ብሔራዊ ጥቅም እና የዜጎች ክብር ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመና በመደርጀት ላይ ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ ይህ ስትራቴጂያዊ ምርጫ ከታዛቢነት ወደ አጀንዳ ተላሚነት እና ተጽዕኖ ፈጣሪነት ለመሸጋገር አስችሎናል ነው ያሉት። ኢትዮጵያ በድንበር ተሻጋሪ ሀብቶቿ ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ስትቀበል፤ በዛው…
ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ የመንግሥትን የ2018 በጀት ዓመት እቅድ በሁለቱ ም/ቤቶች መክፈቻ ሥነ ሥረዓት ላይ ማቅረብ ጀምረዋል
ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና በፌዴሬሽን ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ የፌደራል መንግሥቱን ዓመታዊ ዕቅድ ማቅረብ ጀምረዋል። በሥነ ሥርዓቱ ላይ የሁለቱ ምክር ቤቶች አባላት፣ የሃይማኖት አባቶች፣ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ የተለያዩ ሀገራት ዲፕሎማቶች፣ የክልል ርዕሰ መስተዳድሮችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የሁለቱ ምክር ቤቶች የሥራ ዘመን የጋራ መክፈቻ ሥነ – ሥርዓት ተጀመረ
6ኛው የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽን ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የጋራ መክፈቻ ሥነ – ሥርዓት ተጀምሯል። የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት ተጠሪዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ታዋቂ ሰዎች፣ የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዥ እንግዶች በሁለቱ ምክር ቤቶች የጋራ መክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ ተገኝተዋል።
የኢቲቪ ፓርላማ ቻናል ተመረቀ
የኢቲቪ ፓርላማ ቻናል በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በይፋ ተመርቋል። በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የምክር ቤቱ ምክትል አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ሎሚ በዶ፣ በምክር ቤቱ የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)፣ የኢቢሲ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ቢኒያም ኤሮን ጨምሮ ሌሎች የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች እና ጥሪ…
የሕዝብ ተወካዮችና የፌዴሬሽን ም/ቤቶች 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን መክፈቻ ሥነ ሥርዓት ነገ ይካሄዳል::
6ኛው የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤትና የፌዴሬሽን ም/ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን መክፈቻ ሥነ ሥርዓት በነገው ዕለት ይካሄዳል። የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የአንድ ዓመት የሥራ ጊዜ ከመስከረም ወር የመጨረሻ ሳምንት ሰኞ እስከ ሰኔ 30 ቀን ድረስ መሆኑ ተደንግጓል፡፡ በዚህ መሰረትም የ6ኛው ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የተጠናቀቀ ሲሆን÷ 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት…
የሆረ ሀርሰዴ ኢሬቻ በዓል በስኬት መጠናቀቁን አባ ገዳ ጎበና ሆላ አስታወቁ::
የቱለማ አባ ገዳ ጎበና ሆላ፥ የሆረ ሀርሰዴ ኢሬቻ በዓል ባህላዊ እሴቱን በጠበቀ መልኩ በድምቀት ተከብሮ መጠናቀቁን አስታውቀዋል። አባ ገዳ ጎበና ሆላ የ2018 ዓ.ም የሆረ ሀርሰዴ ኢሬቻ በዓል በስኬት መጠናቀቁን ምክንያት በማድረግ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ፥ በዓሉ ባህላዊ እሴቱን በጠበቀ መልኩ እንዲከበር አስተዋፅዖ ላደረጉ አካላትም ምስጋና አቅርበዋል፡፡
የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ የሆረ ሀርሰዴ ኢሬቻ በዓል በድምቀት እንዲከበር አስተዋጽኦ ያበረከቱ አካላትን አመሰገኑ::
የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ የሆረ ሀርሰዴ ኢሬቻ በዓል በድምቀት እንዲከበር የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበዋል። የሆረ ሀርሰዴ ኢሬቻ በዓል በቢሾፍቱ ከተማ “ኢሬቻ ለሀገር ማንሠራራት” በሚል መሪ ሀሳብ በድምቀት ተከብሯል። በአከባበር ሥነ ሥርዓቱ አባገዳዎች፣ ሀደ ሲንቄዎች፣ ከተለያዩ የኦሮሚያ ክልል አካባቢዎች የመጡ የኅብረተሰብ ክፍሎች እና የውጭ ሀገር ጎብኚዎች ታድመዋል።


