“አዲሱን ዓመት በደስታ አስጀመራችሁኝ ልጆቼንም ሰበሰባችሁልኝ”
እናት ሀምዲያ መሀመድ የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ገንብቶ ያጠናቀቀውን የአቅመ ደካማ ቤት በዛሬው ዕለት ቁልፉን ለባለቤቱ አስረከበ። ቢሮው የራሳቸው 3 ልጆች በተጨማሪ ደግሞ የሚያሳድጓቸው 2 ልጆች በድምሩ የ5 ልጆች እናት የሆኑትን የእናት ሀምዲያ መሀመድ ቤትን ዘመናዊ እና ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ገንብቶ በማጠናቀቅ አስረክቧል። በዚህም በመርሃ-ግብሩ የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት…


