በፌዴራል ስራና ከህሎት ሚኒስቴር ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች እና ባለሞያዎች የተመራ የልዑካን ቡድን በአስተዳደሩ ስራና ከህሎት ቢሮ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎችን ጉብኝት አካሂዷል::

በሚኒስቴር መሰሪያ ቤቱ የኢንዱስትሪ ግንኙነት እና የስራ ሁኔታዎች ቁጥጥር መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ጥኡመዝጊ በርሄ ለተመራው ቡድን የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ እና በቢሮው የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በዘርፉ እየተከናወኑ ሳላሉ ስራዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ከነዚህም መካከል ከስራ እድል ፈጠራ በከተማ እና በገጠር ስለተከናወኑ ሥራዎች እንዲሁም የሞያ ብቃት ማረጋገጫ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥን በተመለከተ ገለፃ ተደርጓል ።

የልኡካን ቡድኑ በመስክ በመገኘት የድሬዳዋ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስልጠና እና ክህሎት አሰጣጠንና እና በወረዳዎች ሰለሚሰጠው የአንድ ማእክል አገልገሎትን በተመለከተ ምልከታ አድርጓል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *