በድሬዳዋ አስተዳደር የሁላሁሉል እና ኮርቱ ገጠር ቀበሌዎች ሜዳ ላይ ከመፀዳዳት ነፃ መውጣታቸው በመረጋገጡ የዕዉቅና እና ሽልማት ተሰጠ፡፡

    በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ በተሰሩ መጠነ ሰፊ ሥራዎች ሜዳ ላይ ከመፀዳዳት ነፃ ለሆኑ ቀበሌዎች የዕውቅና ሽልማት ተሰጠ፡፡ በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ የሃይጅንና አካባቢ ጤና አጠባበቅ ክፍል በአስተዳደሩ ሜዳ ላይ ከመፀዳዳት ነፃ የሆኑ የገጠር ቀበሌዎችን ሽፋን ለማሳደግ እያከናወነ ባለው ዘርፈ ብዙ ትግበራ የሁላ ሁሉል እና የኮርቱ ገጠር ቀበሌዎች ሜዳ ላይ ከመፀዳዳት ነፃ መሆናቸው ታውጇል፡፡ በሁለቱም ገጠር…

    Read More

      ምርጫው ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም እንደሚካሄድ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ::

      ግንቦት 28 ቀን ሊካሄድ የነበረው ሀገራዊ ምርጫ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም እንደሚካሄድ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። ምርጫው የሚካሄደው የመራጮች ምዝገባ በተጠናቀቀባቸው ሁሉም ቦታዎች ብቻ ነው ተብሏል። ከመራጮች ምዝገባ ጋር ተያይዞ አቤቱታ የተነሳባቸው እና ምዝገባውን ዘግይተው የጀመሩ እና ያላጠናቀቁ የምርጫ ክልሎች እና ጣቢያዎች ላይ ግን ምርጫው በተጠቀሰው ቀን እንደማይካሄድ መገለፁን ኤፍቢሲ ዘግቧል።

      Read More

        ሁለተኛው ዙር የህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌት የግብጽ ፍላጎት ላይ ተጽዕኖ እንደማያሳድር የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሜህ ሹክሪ ገለጹ::

        ሁለተኛው ዙር የህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌት የግብጽ ፍላጎት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እንደማያሳድር የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሳሜህ ሹክሪ ተናግረዋል፡፡ ግብጽ ትልቁ የአስዋን ግድብ ክምችት ስላላት በሱ ላይ መተማመን እንደምትችል ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከግማሽ በላይ የሚሆነው ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል ሳያገኝ የሚኖርባትን ኢኮኖሚዋን ለማጎልበት ለፕሮጀክቱ አስፈላጊነት አፅንዖት ሰጥታለች ሲል የዘገበው ኢጅፕት ኢንዲፔንደት ነው፡፡ ምንጭ፦EBC

        Read More

          የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ የሁሉም ባለ-ድርሻ አካላት ርብርብን እንደሚጠይቅ ተገልፃል ።

          6 ተኛውን አለም አቀፍ የመንገድ ደህንነት ሳምንት አስመልክቶ ” መንገድ ለህይወት ” በሚል መሪ ቃል በፍጥነት ምክንያት እየደረሰ ያለውን የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ ይቻል ዘንድ የፌደራል ትራንስፖርት ባለስልጣን ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ በመሆን የውይይት መድረክ አካሂዷል ። በተለይም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በሀገራችን ላይ የትራፊክ አደጋ በብዛት እየደረሰ ይገኛል ። ከዚህም የትራፊክ…

          Read More

            የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የመራጮች ምዝገባ ተራዘመ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የመራጮች ምዝገባ ጊዜን አራዝሟል፡፡

            ቦርዱ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የመራጮች ምዝገባ በኢንተርኔት እንደሚከናወን ማሳወቁ እንዲሁም ይህንን ተከትሎ ምዝገባ ሲከናወን እንደነበር ይታወቃል። በየምርጫ ጣቢያዎቹ የሚደረገው የመራጮች ምዝገባ ቢጠናቀቅም ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ተጨማሪ የምዝገባ ጊዜ መሰጠት እንዳለበት ቦርዱ ወስኗል። በዚህ መሰረት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች እስከ ግንቦት 17 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ https://www.ovrs.gov.et በሚገኘው የመመዝገቢያ አድራሻን በመጠቀም መመዝገብ እንደሚቻል ከቦርዱ…

            Read More

              የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ ተጠናቀቀ::

              650 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኃይል ማስተላለፊያ መሥመር ዝርጋታ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁ ተገለጸ፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኃይማኖት አባቶችና ከሲቪክ ማኅበራት ጋር ግድቡን በተመለከተ ዛሬ ውይይት አድርጓል፡፡ በዚህ ውይይት ላይ የኃይል መሥመር ዝርጋታው ከግድቡ ከተገነባበት ጉባ አንስቶ ብሔራዊ የኤሌክትሪክ ኃይል ቋት እስከሚገኝበት ሆለታ ድረስ ተዘርግቷል ተብሏል፡፡ የግድቡ ተደራዳሪዎች ቴክኒክ ቡድን አባል ዶክተር በለጠ…

              Read More