የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮና የቀበሌ ኮሚኒኬሽን ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሰራር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተጠቆመ::
የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮና በቀበሌ ደረጃ ያሉ የኮሚኒኬሽን ዘርፍ ባለድርሻ አካላት የግንኙነት አግባብና ቅንጅታዊ አሰራር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት በሁለቱ ባለድርሻ አካላት መካከል በተደረገው የምክክር መድረክ ተገልጿል፡፡ በምክክር መድረኩ ቢሮው ያደረገው የመስክ ጉብኝት ሪፖርት የቀረበ ሲሆን የሰው ሃይልና የግብዓት እጥረት፣ የግንኙነት አግባብ መላላት፣የስራ አፈፃፀምን ሪፖርት በወቅቱ አለማቅረብ መስተዋሉን ሪፖርቱን ያቀረቡት የቢሮው ባለሙያና የመስክ ጉብኝቱ…


