አቢቹ አባ መላ ABICHU ABBAA MALAA የኦሮሞ አባ ገዳዎች ህብረት፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ፤ በጦር ግንባር ተሰልፈው ሰራዊቱን በመምራት ላስመዘገቡት ድል “አብቹ አባ ቢያ” የሚል የገዳ ስርዓት የጀግንነት ስያሜ መስጠቱን አስታውቋል።
ህብረቱ ዛሬ ባካሄደው ጉባዔ፤ በከረዩ አባ ገዳ ላይ ጠላት የፈፀመውን ግድያ በጽኑ በማውገዝ፤ ከአሸባሪው ህወሃት ጋር ህብረት የፈጠረ ማንኛውም አካል የኦሮሞ ጠላት እንደሆነ መወሰኑን አስታውቋል። የኦሮሞ አባ ገዳዎች ህብረት ፀሐፊና የቱለማ አባገዳ ጎበና ሆላ፤ የኦሮሞ ህዝብ እንደትናንቱ ሁሉ ዛሬም ከሌሎች ወንድም የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ለሀገር አንድነት የላቀ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ገልፀው፤ “ጠላት ‘ሀገር ፈረሰች’ ብሎ…


