በድሬዳዋ አስተዳደር የአቅመ ደካማ ቤቶችን የማደስ ስነ-ስርአትን ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች አስጀመሩ ።
በድሬዳዋ አስተዳደር ላይ በሚገኙ የተለያዩ አካባቢዎች ለሚኖሩ አቅመ ደካማ የሆኑ እናቶችና አባቶች የሚኖሩባቸውን ቤቶች ከዚህ ቀደም በየአመቱ በክረምት ወራት የበጎ-ፍቃድ ስራዎች ላይ ቤቶቹን አፍርሶ የማደስ ስራዎች ሲሰሩ ቆይተዋል ። በዛሬው እለትም በከተማዋ ላይ የሚኖሩና በአቅም ማነስ ምክንያት በደሳሳ ጎጆ ውስጥ የሚኖሩ አቅመ ደካማ የሆኑ እናቶችና አባቶች ቤቶችን አፍርሶ የማደስ መርሀ-ግብርን ከፍተኛ የአስተዳደሩና የብልፅግና ፓርቲ አመራሮች…


