የድሬዳዋ አስተዳደር ከተማ ስራ አስኪያጅ ፅ/ቤት በታሪፍ ማሻሻያ ባወጣው ረቂቅ መመሪያ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት እካሄደ

የድሬዳዋ አስተዳደር ከተማ ስራ አስኪያጅ ፅ/ቤት የመኝታ አገልግሎት ግብር አሰባሰብ አመዘጋገብና የሪፖርት አቀራረብ መመሪያ ቁጥር 1703/2017 ላይ በዛሬው እለት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል:: በውይይት መድረኩ የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር ከተማ ስራ አስኪያጅ ፅ/ቤት ኃላፊ ኢንጂነር ጀማል ኢብራሂም በዛሬው መድረክ በዋነኝነት የመኝታ ግብር ለማሰባሰብ በወጣው ረቂቅ መመሪያ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመወያየትና ግብአት በማሰባሰብ…

Read More

የፌደራል መንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ከክልሎች ጋር በናበብ የ2017 ዓ.ም እስትራቴጂክ እቅድ ማቀዱ ይታወሳል።

የድሬዳዋ አስተዳደር መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ከፊደራል የወረደውን እስትራቲጂ እቅድ ከአስተዳደሩ ነባራዊ ሁኔታ ጋር በማጣጣም እቅዱን በመከለስ የተቋሙ ኃላፊ አቶ ብሩክ ፈለቀ በተከለሰው እቅድ ላይ ከዳሬክቶሬቶች እና ደጋፊ የስራ ሂደት ጋር ተፈራረሙ። አቶ ብሩክ ፈለቀ በፊርማ ስነ ስርዓት እንደተናገሩት እቅዱ ፈፃሚ ባለሙያዋች ድረስ በማውረድ ለተፈፃሚነቱ ኃላፊነታችንን ልንወጣ ይገባል ብለዋል።

Read More

በሚካሔደው የኮሪደር ልማት ጎዳና ላይ የሚጣል የማህበረሰብ ክፍል የለንም ፦ ከንቲባ ከድር ጁሀር

#DGC መስከረም 20/2017 በድሬዳዋ አስተዳደር በወረዳ 03 አካባቢ የኮሪደር ልማቱ በሚያልፍባቸው አካባቢዎች የሚኖሩ የማህበረሰብ ክፍሎችን የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሀር አወያይተዋል። በውይይቱ የተሳተፉ የወረዳ 03 የልማት ተነሺዎች ጥያቄዎቻቸውን ለከንቲባ ከድር ጁሀር አቅርበዋል፤ ድሬዳዋ ከተማ በልማት ወደኋላ ቀርታለች መልማት አለባት ፤ ልማቷ ግን ህብረተሰቧን ሊጎዳና ጎዳና ሊጥል በሚችል መልኩ መሆን የለበትም ፤ በልማቱ ምክንያት እንድንነሳ የተሰጠን…

Read More

“የከተማ ግብርና ሀገር አቀፉን የምግብ ዋስትና ያጎለብታል”፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

የከተማ ግብርናን ሥራ የከተማ የአኗኗር ዘይቤ ስትራቴጂ አካል አድርገን ስናስፋፋ የማሻገር አቅሙ ላይ ጥርት ያለ መረዳት ይዘን ነበር ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልፀዋል። የከተማ ግብርና የግብርናውን ክፍለ ኢኮኖሚ ከማጎልበቱ ባሻገር የከተማ ምጣኔ ሃብትን እና የሥራ ፈጠራን ያሳድጋል። ሀገር አቀፉን የምግብ ዋስትና ያጎለብታል። የከተማ ልማት ሥራን ይደግፋል። ተጠቃሚዎችን በቀጥታ ከአምራች የአካባቢው ገበሬዎች ጋር ያገናኛል።…

Read More

ድሬዳዋ ከተማ ወላይታ ድቻን በማሸነፍ የሊጉ መሪ ሆኗል

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሁለተኛ ሳምንት ጨዋታ ድሬዳዋ ከተማ ወላይታ ድቻን 4 ለ 1 አሸንፏል። በድሬዳዋ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ዩጋንዳዊው ቻርልስ ሙሲጌ እና መሐመድ ኑር ናስር በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን ለድሬዳዋ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ያሬድ ዳርዛ ለወላይታ ድቻ በ75ኛው ደቂቃ ብቸኛዋን ግብ አስቆጥሯል። ውጤቱን ተከትሎ ድሬዳዋ ከተማ በስድስት ነጥብ የሊጉ መሪነት ይዟል። ተጋጣሚው ወላይታ ድቻ በውድድር ዓመቱ…

Read More

#ዜና የ5 ሚሊዮን የኮደርስ ስልጠና ለድሬዳዋ ነፃ የንግድ ቀጣና ልዩ በረከት ነው – ከንቲባ ከድር ጁሀር

#DGC መስከረም 18/2016 የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና ኢንሸቲቭ የድሬዳዋ ነፃ የንግድ ቀጣናን የኦን ላይን ግብይት ለማቀላጠፍ መልካም እድል መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሀር ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የ”5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ” በ2026 አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን በዌብ ፕሮግራሚንግ፣ አንድሮይድ ማበልፀግ፣ ዳታ ሳይንስና በሰው ሰራሽ አስተውሎት መሠረታዊ የዲጂታል ክህሎት የማስጨበጥ አላማ ያለው ነው።…

Read More

በቀን 150 ሺህ ኩንታል የማምረት አቅም ያለውን የለሚ ብሔራዊ የሲሚንቶ ፋብሪካ መርቀን ሥራ አስጀምረናል።

ይህ ሜጋ ፕሮጀክት የመንግሥታችን በፍጥነት፣ በግዝፈት እና በንፅህና የመገንባት ጽኑ አቋማችን የማሳያ ነው። እጅግ አስፈላጊ የሆኑ መሠረተ ልማቶችን በፍጥነት እና በብቃት አጠናቅቆ ዝግጁ የማድረግ ተምሳሌትም ነው። ይህ በአሁኑ ወቅት በመላ ሀገራችን ያሉ ተመሳሳይ ፋብሪካዎች ተደምረው የሚያመርቱትን ሃምሳ ከመቶ የሚያመርት ፋብሪካ እውን እንዲሆን የተሳተፋችሁ በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ። ከሁለት አመታት በኋላ ወደዚህ ስፍራ ስመለስ የአመራር መርሆዎቻችን…

Read More