“በከተማና በገጠር የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎችን አቀናጅተናል። እንዲሁም ነባር የጎብኚ መዳረሻዎችን አሻሽለናል። አዳዲስ መዳረሻዎችንም አልምተናል። እነዚህ ሁሉ በተለየትኩረት ከሠራንባቸው የለውጥ ማሳያዎች መካከል ጥቂቶቹ ናቸው።
ሀገራችን ከዚህ በፊት ከነበሯት የጎብኚ መዳረሻዎች ላይ በእነዚህ ጥቂት ዓመታት ብዙ ጨምረናል። መዳረሻዎቹም መላው ሀገራችንን ያካለሉ ናቸው። ከሀገራችን ስፋትና ከመብዛት አንጻር ያልደረስንባቸውና በዕቅድ ላይ ያሉ ብዙ መዳረሻዎችም በቀጣይ ይገነባሉ። በእጃችን ላይ ያሉ የጎብኚ መዳረሻዎችን በሚገባ አገልግሎት ላይ ማዋልና ከዚህም ሊገኝ የሚችለውን ሀገራዊ ጥቅም ሁሉ መሰብሰብ ተገቢና በቀጣይ ለምንጓዘው አቅጣጫ ትልቅ ግብዓት የሚሆን ነው። ከዚህ አንጻርም…


