ኑ ተማሪዎች ላፍታም ሳንዘናጋ ሁላችንም ወደ ትምህርት ቤታችን እንመለስ!!!

    የነገ የሀገር ተስፋ የሆናችሁ ተማሪዎች ይህችን መተኪያ የሌላትን ሀገር ካላት ራዕይ ጭምር የምትረከቡ እናንተ ናችሁ፡፡ ወላጆቻችሁ እና ሀገራችሁ ከእናንተ ብዙ ይጠብቃሉ፡፡ ከእናንተ የሚፈለገውን ሁሉ መውጣት እንድትችሉ ትምህርት የማይተካ ቁልፍ ሚና አለው፡፡ ትምህርት ለሀገር ዕድገት ቁልፍ ነውና፡፡ ስለሆነም በኮቪድ-19 ምክኒያት ተቋርጦ የነበረው ትምህርት በአስተዳደራችን በሚቀጥለው ሳምንት ሙሉ በሙሉ ይጀምራል፡፡ ለአፍታም ሳንዘናጋ ሁላችንም ወደ ትምህርት ቤታችን እንመለስ፡፡…

    Read More

      በአስተዳደሩ የንፁህ ውሃ መጠጥ ለደንበኞች የማዳረስ ሥራዎች በዚህ ዓመት ከ5 ሺህ አዳዲስ ደንበኞች ተጠቃሚ ይሆናሉ ተባለ፡፡

      የድሬዳዋ አስተዳደር የከተማ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን የደንበኞች ፎረም መድረክ አካሄደዋል፡፡ የድሬዳዋ ከተማ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ለደንበኞች የሚሰጠውን አገልግሎት አሁን ካለበት ደረጃ በተሻለ በልኩ ለማሳደግ እንዲችል እስከ አሁን ያለውን ልምድ እና በቀጣይ የሚገኘውን ልምድ በመቀመር የመረጃ መለዋወጥ ስርዓቱን በተጠናከረ መልኩ በተቋም ደረጃ የደንበኞችን አገልግሎት አሰጣጥ መሳለጥ እንቅፋት የሆኑ አሰራሮችን ለባለስልጣኑ በመጠቆም እንዲወገዱ የሚያስችል ተግባራት እንደሚቀጥሉ ተገልጸዋል፡፡…

      Read More

        በታላቅ ድምቀት የሚከበረውን የቁልቢ ገብርኤል በአለ ንግስ ያለምንም የፀጥታ ችግርና የወንጀል ተግባር ብሎም የትራፊክ አደጋ ሳይከሰት በሰላም እንዲከበር ለማስቻል ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን የድሬደዋ ፖሊስ ገለፀ ፡፡

        ከበአሉ ጋር ተያይዞ መግለጫ የሰጡት የኮሚሽኑ የወንጀል መከላከል ዘርፍ ሃላፊ ኢ/ር አንተነህ ረፌራ እንዳስታወቁት በዓሉ ሰላማዊ በሆነ መልኩ እንዲከበር ለማስቻል ለሁሉም ፈፃሚ አመራር እና አባላት እንዲሁም አጋዥ ተቋማት ቀደም ባሉት ቀናት የበአሉን አከባበር የተመለከተ የፀጥታ እቅድ ወቶ በቂ ግንዛቤ እንዲጨብጡ ከማድረግ ጀምሮ ሌሎች የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ሲሰሩ እንደነበር ገልፀው አሁን ላይ በአሉ ያለምንም የፀጥታ ችግርና…

        Read More

          የድሬዳዋ አስተዳደር መሬት ልማት ማኔጅመንት ቢሮ በመሬት ነክ የህግ ድንጋጌዎች ዙሪያ ምክክር አካሂዷል፡፡

          በምክክር መድረኩ ላይ የመክፈቺያ ንግግር ያደረጉት የመሬት ልማት ማኔጅመንት ቢሮ ሃላፊ አቶ ገበየሁ ጥላሁን እንደገለፁት መድረኩን ያስፈለገበትን ምክንያት ሲገልፁ በተቋማት መካከል ቅንጅታዊ አሰራሪን በማጠናከር ከመሬት ጋር ተያይዞ ህጋዊ አካሄድን የተከተለ ቀልጣፋ፤ፍትሃዊ፤ዘመናዊ አገልግሎት ለህዝቡ በመስጠት ከመሬት ጋር የተያያዘዉን የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ችግሮች መፍታት እንዲቻል ታስቦ የተዘጋጀ መድረክ መሆኑን አስገንዝበዋል። በምክክር መድረኩ ላይ የሊዝ አዋጅ ምንነትና በአዋጁ…

          Read More

            6ኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ ግንቦት 28 ቀን 2013 ዓ.ም እንዲሆን ሃሳብ ቀረበ::

            በተያዘው ዓመት የሚካሄደው 6ኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ የድምፅ መስጫ ቀን ግንቦት 28 ቀን 2013 ዓ.ም እንዲሆን ሀሳብ ቀረበ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር የምርጫ ረቂቅ የጊዜ ሰሌዳን አስመልክቶ የምክክር መድረክ እያካሄደ ነው።

            Read More

              በድሬዳዋ አስተዳደር ገቢዎች ባለስልጣን ከ160 በላይ ለሆኑ ለደረጃ ሀ ግብር ከፋዮች ስልጠና ሰተዋል። ከ14/04/2013 ዓም እስከ 16/04/2013 ዓም ድረስ ለደረጃ ሀ ግብር ከፋዮች ::

              ለሆቴል፣ግሮሰሪ፣ለልኳንዳቤቶች፣ህንፃ መሳሪያ፣ ስፔር ፓርት እና ሌሎች ዘርፍ ላይ በሂሳብ መዝገብ አያያዝ መመሪያ ዙሪያ ግንዛቤ ማስጨበጫ የተሰጠ ሲሆን ከሂሳብ ሰነድ አያያዝ እስከ ሂሳብ መግለጫ ያለውን ያጠቃለለ ነው። ዘርፉ በከፍተኛ ሁኔታ ግብይት ስለሚካሄድበት በዘርፉ ያለውን በደረሰኝ ያለመገበያየት ችግርንም ለመቅረፍ የሚረዳ መሆኑ ይታወቃል። በስልጠናዉ ላይ የግብር አንባሳደሮቻችን ስለ ግብር መክፈል መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

              Read More

                ሀገር ዓቀፍ የወባ ሳምንት ዘመቻ በይፋ ተጀመረ፡፡

                አንደ ፈረንጆቹ አቆጣጠር በ2030 እንደ ሀገራችን ደግሞ በ2023 ዓ/ም የወባ በሽታን ለማጥፋት በተያዘው ዕቅድ መሰረት ይህንኑ ዕቅድ ተግባራዊ ለማድረግ የሚረዳ ሀገር ዓቀፍ የወባ ሳምንት ዘመቻ በይፋ ተጀምሯል፡፡ የዘመቻውን መጀመር ይፋ ያደረጉት የከንቲባው የማህበራዊ ዘርፍ አማካሪ ተወካይ አቶ መሃመድ አሚን እንደተናገሩት ‹‹በአስተዳደራችንም ይሁን እንደ ሀገር ያለውን የወባ በሽታ ስርጭት ለማስወገድ የሚረዱ ተግባራትን በተለያዩ ጊዜያት በሚካሄዱ ሥራዎች…

                Read More