የድሬዳዋ አስተዳደር ገቢዎች ባለስልጣን በ2013 በጀት ዓመት በህዳር ወር የመንግስት ግብር 96.39% እቅዱን ማሳካቱን እና በአምስት ወራት ውስጥ ከ581 ሚሊዬን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን ገልፇል።
የድሬዳዋ አስተዳደር ገቢዎች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዱሰላም መሐመድ የአምስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀም አስመልክተው አጭር መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ ባለስልጣን መ/ቤቱ በ2013 በጀት ዓመት በአምስት ወር ከመንግስት ታክስ እና ከመዘጋጃቤታዊ ገቢ ብር 746,686,895.38 ለመሰብሰብ አቅዶ ብር 581,401,743.19 መሰብሰብ የቻለ ሲሆን ክንውኑ ከዕቅዱ ጋር ሲነፃፀር 77.86በመቶ አፈፃፀም አለው፡፡ ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም የ2013 በጀት ዓመት የአምስት ወራት አፈፃፀም ከ2012…


