” ጽዱና ዉብ ከተማ እንድኖረን ከፈለግን ቁሻሻን የሚጸየፍ መህበረሰብ ማፍራት አለብን” የድሬዳዋ አሰተዳደር ብልጽግና ጽ/ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ
በአሰተዳደራችን በ15 ቀን አንዴ የሚካሄደዉ ከተማ አቀፍ የጽዳት ዘመቻ ዛሬ ለ33ኛ ጊዜ የተካሄደ ሲሆን በቀበሌ 01አሰተዳደር ከ መልካ ወደ ኢንዱስትሪ ፓርክ የሚወሰደዉ አሰፓልት መንገድ የአሰተዳደራችን ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጁሃርን ጨምሮ በ ካቢኔ ደረጃ ያሉ ከፍተኛ አመራር እሰከ ቀበሌ አመራር ደረጃ ያሉ የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም በተለያዩ በጎ ተግባር ላይ የሚሳተፉ የወጣት ማኀበራት አባላት በተገኙበት ለሁለት…


