የመሬት ልማትና ማኔጀመንት ቢሮ በ2015 በጀት አመት ህገወጥ የመሬት ወረራን ለመከላከል ትኩረት ሊሠጥበት እንደሚገባ ተገለጸ። ቢሮው የ2014 እቅድ የአፈጻጸም ሪፖርት እና የ2015 በጀት አመት እቅዱን በህዝብ ክንፍ አስገምግሟል።

    በመድረኩም ከአስተዳደሩ የተውጣጡ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች የተሳተፋ ሲሆን የአፈጻጸም ሪፖርትና እቅድ ቀርቦ ሠፊው ውይይት ተካሂዷል። ከመድረኩም ቢሮው እያከናወነ በሚገኘው የሪፎርም ስራ እያመጣ ያለው ለውጥ አበረታች መሆኑ የተጠቀሰ ሲሆን በቀጣይም የተቋቋመለትን አላማ ከዳር ለማድረስና የህብረተሰቡን ቅሬታው ከመቀነስ አኳያ ይበልጥ መንቀሳቀስ እንደሚገባ ተመላክቷል። በተጨማሪም መረጃን ከኢንፎርሜሽን ኮምንኬሽን ቴክኖሎጂና ጋር ለማስተሳሰር እየተከናወነ የሚገኘው ተግባር ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተገልጿል።…

    Read More

      የኤልፍሬድ ሻፊ ድልድይ Riqicha Alfered shafi Bundada Elfered Shafi የድሬደዋ ትልቁ ድልድይ ከከዚራ ወደ ኮኔል የሚያሻግረው በተለምዶ ዳቻቱ ድልድይ ተብሎ የሚጠራዉ በ1962—-1963 ዓ/ም በያኔዉ አጠራር በድሬደዋ አውረጀ አገረ ገዥ ና ማዛገጀቤታዊ ሹም በነበሩ በአቶ አልፈሪድ ሻፊ አስተደደር የተሠረ ድልድይ መሆኑን ታሣቢ በማድረግ በዛሬዉ እለት ከፍተኛ የፌድራልና የአሰተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት አልፍሬድ ሻፊ ድልድይ ተሰይሟል

      Read More

        ለክቡር አርቲስት ዶ/ር አሊ ቢራ በስሙ ፓርክ ተሰየመ

        ዛሬ ሀምሌ 14 ቀን 2014 ዓ.ም ለክቡር አርቲስት አሊ ቢራ ዶ/ር በስሙ ፓርክ መሰየሙን የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ ከድር ጁሃር አብስረዋል፡፡ ክቡር ከንቲባ ከድር በቦታው ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት በአገራችን የሙዚቃ ስራ ውስጥ እንደተወደደ እና እንደተከበረ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ታዋቂ ሆኖ የኖረውን ታላቁ የሙዚቃና የፍቅር ሰው ለክቡር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ መታሰቢያ ለመሰየም በመገኘቴ ከልብ…

        Read More

          በናፍቆት የድሬዳዋ ሳምንት የደም-ልገሳና የህፃናት መዝናኛ መርሀ-ግብሮች ተካሄደ ።

          በድሬዳዋ አስተዳደር ከሀምሌ 11 እስከ ሀምሌ 16 2014 ዓ.ም ድረስ ናፍቆት የድሬዳዋ ሳምንት በተለያዩ መርሀ-ግብሮች በታላቅ ድምቀት እየተከበረ ሲሆን በዛሬው እለትም ልጆችንና ቤተሰቦችን አሳታፊ ያደረጉ የተለያዩ መርሀ-ግብሮች ከመካሄዳቸውም በዘለለ የደም ልገሳ ፕሮግራምም ተካሂዷል ። በነዚህም መርሀ-ግብሮች ላይ ተሳታፊ የሆኑ አካላት በበኩላቸው በናፍቆት የድሬዳዋ ሳምንት ላይ በሚካሄዱት ፕሮግራሞች ላይ በመሳተፋቸው ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረው በቀጣይም እንደዚህ አይነት…

          Read More

            የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት ኢኮኖሚ እና ኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከአስተዳደር ምክር ቤት የህዝብ ክንፍ ጋር የድሬዳዋ አስተዳደር የ2015 በጀት አመት ረቂቅ በጀት ዙሪያ ውይይት አካሂዷል፡፡

            በምክር ቤቱ የመሰብሰቢያ አዳራሽ በተካሄደው የውይይት መድረክ ላይ የአስተዳደር ምክር ቤት የበጀት ኢኮኖሚ እና ኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ አይናለም ተዘራ ባደረጉት ንግግር የሚመደበው በጀት በአግባቡ ስራ ላይ እንዲውል የተለያዩ ተቋማት የፋይናንስ አጠቃቀምን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ ከፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ጋር በመሆን የተቀናጀ ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው የህዝብ ክንፍ አባላቱም ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት…

            Read More